Monday, February 24, 2014

GOLD, CORRUPTION AND HUMAN RIGHTS




በዓመት 3500 ኪሎ ወርቅና እና 4500 ኪሎ ብር (silver) ከኢትዮጵያ እንደሚረከብ በስዊዝ Argor Heraus Refinery የተባለው የወርቅ ማጣሪያ ኩባንያ አስታወቀ። የወርቁ ባለቤት ሼክ መሃመድ አላሙዲ፣ ባለቤታቸው ወ/ሮ ሶፍያ ሳላ አለሙዲ እና የኢትዮጵያ መንግስት መሆናቸውን በድህረ ገፁ አሳውቋል። Argor-Heraeus Refinery የተባለው የስዊዝ ኩባንያ በኮንጎ ጦርነት ወከባ የተዘረፈ ህገ ወጥ ወርቅ በማከማቸቱ ክስ ላይ ይገኛል።

ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግስት ለጌ ደምቢ የሚባለውን የወርቅ ማውጫ ገደል በ172 ሚሊዮን ዶላር ለሃያ አመታት ለሼክ መሃመድ መሸጡን ድህረ ገፁ ቢናገርም በኢትዮጵያ መንግስት በዚህ ጉዳይ ላይ የተነገረው ነገር የለም። ከለጌ ደምቢ 6500 ኪሎ በዓመት ወደ ስዊዝ Argor Heraus Refinery የተባለው የወርቅ ማጣሪያ እንደሚያስረክብ ድህረ ገፁ ይናገራል።
በአጠቃላይ ሼክ መሃመድ እና የኢትዮጵያ መንግስት በአመት 10000 kg ወርቅ ወደ ስዊዘርላንድ ይልካሉ ማለት ነው።

No comments:

Post a Comment