Thursday, May 30, 2013

የአሜሪካ የህግ ባለሙያዎችና አኢጋን ጋራ በኅብረት ስራ ጀመሩ!

የአሜሪካ የህግ ባለሙያዎችና አኢጋንጋራ በኅብረት ስራ ጀመሩ!

በኢትዮጵያ በግፍ የታሰሩ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን በተመለከተ የአሜሪካን የህግ ባለሙያዎች ማህበር (ABA – American Bar Association) ሙሉ በሙሉ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችለውን ስራ አርብ እንደሚጀምር ተገለጸ። አዲስ አበባ ካሉ የፖለቲካና የሙስሊም ወገን እስረኞች ጠበቆች ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ አርብ ግንቦት 23፤2005ዓም ያደርጋሉ። አቶ ኦባንግ ሜቶ የተረሱ እስረኞች ጉዳይም እንደሚካተት ጠቅሰው በፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ ለታሰሩ ዜጎች ጥብቅና የቆሙ ካሉ የአዲሲቷን ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ በቀጥታ እንዲገናኙ ጥሪ አቅርበዋል
(ABA) በሚል ስያሜ የሚታወቀውና ከተቋቋመ 135ዓመታትን ያስቆጠረው የአሜሪካ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር ከ400 ሺህ በላይ የህግ ባለሙያ አባላት አሉት። ይህ በአሜሪካ ትልቅ የተባለ ማህበር በግፍ ለሚሰቃዩ ኢትዮጵያዊያን እስረኞች ድጋፍ ለማድረግ የወሰነው የአኢጋን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ በይፋ የድጋፍ ጥያቄ ባቀረቡ በቀናት ውስጥ ሲሆን፣ በጋራ በተከናወኑ ንግግሮችና የሰነድ ውይይቶች በወር ጊዜ ውስጥ ወደ እንቅስቃሴ ለመግባት እንደተቻለ ለማወቅ ተችሏል
በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ ኢህአዴግ ህግን ከለላ በማድረግ በዜጎች ላይ የሚፈጽመውን ግፍና ወንጀል፣ ለአፈና ተግባሩ ማስፈጸሚያም የጸረ ሽብርተኝነትን፣ የመያዶችን፣ ወዘተ ህጎችን በማውጣት ዜጎችን ለወህኒ ቤትና ለቁም እስር፣ ለስደት፣ ለስቃይ መዳረጉን፣ የፍትህ አካላቱን ህግን በሚያከብሩና ፍትህ በሚያስፈጽሙ ገለልተኛ አካሎች ሳይሆን ራሱ በመሠረተው ተቋም እያመረተ የሚጠቀምባቸው የፖለቲካው መሳሪያዎቹ ስለመሆናቸው፣ በመዘርዘርና ማስረጃ በማጣቀስ አቶ ኦባንግ ለጉባኤው መናገራቸውን አመልክተዋል።
ቀደም ሲል ጀምሮ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የስራ አስፈጻሚዎች የሚታወቁትም ሆነ ሚዲያው የዘነጋቸው ዜጎች ጉዳያቸው ዓለም ዓቀፍ ትኩረት እንዲያገኝ በያቅጣጫው እየተደረገ ካለው የተለያየ  ጥረት በተጨማሪ ሲመክርበት የነበረው ጉዳይ እንደሆነ በመግለጽ አስተያየታቸውን የሰጡት አቶ ኦባንግ “ተጽዕኖ ሊፈጥሩ የሚችሉት አካላት በራሳቸው ሰዎች በቂ መረጃ እንዲያገኙ ማድረግ ታላቅ ተግባር ነው። ድርጅታችን እንደ ስኬት ይቆጥረዋል። ዓርብ በዝርዝራችን ካገኘናቸው የታዋቂ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ መሪ ጠበቆች ጋር የስካይፕ ስብሰባ ይካሄዳል። በቀጣይ አገር ቤት በመሄድ ባመቻቸው መንገድ ስራቸውን ያከናውናሉ” ብለዋል።
በአሁኑ ጊዜ በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ የሙስሊሙን ህብረተሰብ ጥያቄ በማንሳታቸው የታሰሩት ወገኖች፣ ወዘተ ጠበቆች ጋር በስካይፕ ንግግር እንደሚደረግ አቶ ኦባንግ አስታውቀዋል። እስከዛሬ ጆሮ ያልተሰጣቸው ወገኖች ጉዳይ አደባባይ ከማውጣት በተጨማሪ የጋራ ንቅናቄው ባቋቋማቸው ግብረኃይሎች አማካይነት ወደ ህግ የሚሄዱ፣ ሌሎች አብረው መስራት የሚፈልጉ አካላት የሚያቀርቧቸውን አገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ጉዳዮች በአገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ክስ መስርቶ ለመሟገት ማህበሩ ዝግጁ መሆኑንን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “አስፈላጊውን የህግ ድጋፍ የሚፈልጉ ድርጅቶችም ሆኑ ግለሰቦች ጥያቄያቸውን ለጋራ ንቅናቄው ማቅረብ ይችላሉ” ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል::
“… ኢህአዴግ በስደተኛነት ስም ደጋፊዎቹን በስርዓቱ የተገፉ በማስመሰል የሃሰት ማስረጃ እያስጨበጠ  በአሜሪካ፣ በካናዳና በተለያዩ የምዕራብ አገራት ያሰማራቸውና በተቀነባበረላቸው መረጃ የስደት መኖሪያ ፈቃድ ካገኙ በኋላ ስደተኛውን እንዲሰልሉና ለሥርዓቱ እንዲሰሩ እያደረገ መሆኑ፤ በተለያዩ አገራት በገቢር የተያዙ መረጃዎችና ዋቢ ክስተቶች መኖራቸውን የተረዳው የባለሙያዎቹ ማኅበር ጉዳዩን በጥልቀት እንደሚያየውና ያለውን ከፍተኛ የሰው ኃይል በመጠቀም ከአኢጋን ጋር እንደሚሰራ ከሌሎች ማኀበራት ጋር በመሆንም በተለይ በምዕራቡ ዓለም የተሰገሰጉትን አስመሳይ ስደተኞች ወደ ፍትህ የማምጣቱ ጉዳይ ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን ለድርጅታቸው አረጋግጠዋል” በማለት ከዚህ ቀደም ለጎልጉል ስለተናገሩት አስተያየት እንዲሰጡ አቶ ኦባንግ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።
“ኢህአዴግን የሚደግፉ ዜጎችም ቢሆኑ ለጋራ ንቅናቄያችን ልጆቹ ናቸው” በማለት አስተያየታቸውን የጀመሩት አቶ ኦባንግ “ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ጉዳይ ላይ ምስጢረኛ ለመሆን እገደዳለሁ። አንድ ነገር ለማስታወስ ያህል ግን ምዕራባውያን አሠራራቸው መጭበርበሩን ካረጋገጡ ምህረት የላቸውም። ከሰብአዊነትም አንጻር ቢሆን አገሩ መኖር ያልቻለን ዜጋ ስደት አገር ድረስ እየተከታተሉ ማሳደድ በየትኛውም መስፈርት ተቀባይነት የለውም። በህግም አይፈቀድም። እንደዚህ ካሉት ጋር የሚተባበሩ አገሮችን ህግ ፊት በማቆም በህግ ስለፍትህ እንከራከራል” የሚል መልስ ሰጥተዋል።
ABA የሚባለው የህግ ባለሙያዎች ማህበር ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ከሁለት ሳምንት በፊት ሲያከብር ንግግር እንዲያደርጉ የተጋበዙት አቶ ኦባንግ ሜቶ በርካታ ጉዳዮችን በማንሳት ድጋፍ ጠይቀው አዎንታዊ ምላሽ እንዳገኙ፣ ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል። አቶ ኦባንግ እንደሚሉት አርብ የሚደረገው ንግግር የድጋፉና አብሮ የመስራቱ ሂደት መጀመሪያ ነው። ሥራው ጊዜ የሚወስድና እልህ የሚያስጨርስ መሆኑን ሁሉም እንዲያስተውለውና ፈጣን ውጤት በመጠበቅ ቶሎ ተስፋ ከመቁረጥ ይልቅ ሁሉም ዜጋ አለኝ የሚለውን መረጃ ለጋራ ንቅናቄው በመላክ ትብብሩን እንዲቀጥል ጨምረው ገልጸዋል፡፡

Saturday, May 25, 2013

Ethiopia:One of the most abusive regime in the world...


The human rights situation in Ethiopia, the most important strategic and security ally of the Western powers, has worsened drastically, according to the 2013 Human Rights Watch’s World Report, which summarizes the human rights situation of more than 90 countries worldwide—drawing on events from the end of 2011 through November 2012.
The 665 page report says that Ethiopia’s dictatorial regime has deliberately continued to severely restrict fundamental rights of freedom of expression, association, and assembly. In addition, the report indicates that intimidation, arbitrary arrest, torture, forced displacement, and killing remain routine throughout the country.
The report, which reflects extensive investigative work that Human Rights Watch undertook in collaboration with local human rights activists, was released in the beginning of February 2013. Providing heartbreaking examples, cases, and photographs, the report explains enough how dramatically the human rights crisis in Ethiopia has been worsening.
Source: Human Rights Watch World Report 2013,  pp 114-120

Thursday, May 23, 2013

" The truth behind the PM Meles Zenawi death"


The death of Prime Minister Meles Zenawi in August in a Belgian hospital brought an end to a 21-year rule characterized by repression of dissent and iron-fisted control of the independent press. His fatal illness was shrouded in secrecy. After Meles disappeared from public view in June, the government played down rumors of his illness and suppressed in-depth domestic reporting. The government also faced rare demonstrations by members of the Muslim community, who protested what they called government interference in their affairs. Security forces violently dispersed the gatherings, cracking down on journalists who reported on them, and  The government drew widespread international condemnation for the convictions of nine Ethiopian journalists on vague and politicized terrorism charges. The journalists, five of them exiles tried in absentia, were handed sentences ranging from eight years to life imprisonmentMore than 70 newspapers were forced to close because of government pressure during the 21 years of Meles' rule. according to CPJ research


The authorities arrested members of political opposition parties, and other perceived or actual political opponents. Arbitrary detention was widespread.
According to relatives, some people disappeared after arrest. The authorities targeted families of suspects, detaining and interrogating them. The use of unofficial places of detention was reported.
  • In January the All Ethiopian Unity Party called for the release of 112 party members who, the party reported, were arrested in the Southern Nations, Nationalities and Peoples (SNNP) region during one week in January.
Hundreds of Oromos were arrested, accused of supporting the Oromo Liberation Front.
  • In September, over 100 people were reportedly arrested during the Oromo festival of Irreechaa.
Large numbers of civilians were reportedly arrested and arbitrarily detained in the Somali region on suspicion of supporting the Ogaden National Liberation Front (ONLF).
  • The authorities continued to arbitrarily detain UN employee, Yusuf Mohammed, in Jijiga. His detention, since 2010, was reportedly an attempt to get his brother, who was suspected of links with the ONLF, to return from exile.
Between June and August, a large number of ethnic Sidama were arrested in the SNNP region. This was reportedly in response to further calls for separate regional statehood for the Sidama. A number of arrests took place in August around the celebration of Fichee, the Sidama New Year. Many of those arrested were detained briefly, then released. But a number of leading community figures remained in detention and were charged with crimes against the state.according to  Amnesty International 2013 Report: Ethiopia .
 After knowing all of these facts and evidences of horrible crimes committed by the EPRDF regime it is beyond me to comprehend why the West or any country that declares to be democratic continues its relationship with this criminal regime.

What is the point of having Amnesty International if the west keeps ignoring those compiled reports of crimes happening on a daily bases against Ethiopians. When is the West going to stop funding those abuses?

Without the West’s fund EPRDF would not have been able to do that.
The EPRDF government in Ethiopia is obsessed and has been abusing and torturing citizens and violating their basic human rights since the last 21 years. EPRDF is not a government but a group of mafias from Tigray ethic that controls the army, the economy, power, the courts and the country’s land.
How can any country accepts this as a regime when it is totally obsessed with controlling everything and leaving nothing to citizens? Where is the people to work, speak freely, the right to own property, peaceful protest and live on the land they cultivated and developed? How can anyone say Ethiopia is my country when they have nothing to claim theirs and he or she is owned by on ethnic group?





Amnesty International 2013 Report: Ethiopia

Amnesty International 2013 Report: EthiopiaThe state stifled freedom of expression, severely restricting the activities of the independent media, political opposition parties and human rights organizations. Dissent was not tolerated in any sphere. The authorities imprisoned actual and perceived opponents of the government. Peaceful protests were suppressed. Arbitrary arrests and detention were common, and torture and other ill-treatment in detention centers were rife. Forced evictions were reported on a vast scale around the country


Background
In August, the authorities announced the death of Prime Minister Zenawi, who had ruled Ethiopia for 21 years. Hailemariam Desalegn was appointed as his successor, and three deputy prime ministers were appointed to include representation of all ethnic-based parties in the ruling coalition.
The government continued to offer large tracts of land for lease to foreign investors. Often this coincided with the “villagization” programme of resettling hundreds of thousands of people. Both actions were frequently accompanied by numerous allegations of large-scale forced evictions.
Skirmishes continued to take place between the Ethiopian army and armed rebel groups in several parts of the country – including the Somali, Oromia and Afar regions.
Ethiopian forces continued to conduct military operations in Somalia. There were reports of extrajudicial executions, arbitrary detention, and torture and other ill-treatment carried out by Ethiopian troops and militias allied to the Somali government.
In March, Ethiopian forces made two incursions into Eritrea, later reporting that they had attacked camps where they claimed Ethiopian rebel groups trained (see Eritrea entry).Ethiopia blamed Eritrea for backing a rebel group that attacked European tourists in the Afar region in January.
Freedom of expression
A number of journalists and political opposition members were sentenced to lengthy prison terms on terrorism charges for calling for reform, criticizing the government, or for links with peaceful protest movements. Much of the evidence used against these individuals consisted of examples of them exercising their rights to freedom of expression and association.
The trials were marred by serious irregularities, including a failure to investigate allegations of torture; denial of, or restrictions on, access to legal counsel; and use of confessions extracted under coercion as admissible evidence.
  • In January, journalists Reyot Alemu, Woubshet Taye and Elias Kifle, opposition party leader Zerihun Gebre-Egziabher, and former opposition supporter Hirut Kifle, were convicted of terrorism offences.
  • In June, journalist Eskinder Nega, opposition leader Andualem Arage, and other dissidents, were given prison sentences ranging from eight years to life in prison on terrorism charges.
  • In December, opposition leaders Bekele Gerba and Olbana Lelisa were sentenced to eight and 13 years’ imprisonment respectively, for “provocation of crimes against the state”.
Between July and November, hundreds of Muslims were arrested during a series of protests against alleged government restrictions on freedom of religion, across the country. While many of those arrested were subsequently released, large numbers remained in detention at the end of the year, including key figures of the protest movement. The government made significant efforts to quash the movement and stifle reporting on the protests.

Wednesday, May 22, 2013

Oromo political prisoners in the Ethiopian Empire !





Oromo political leaders, Obbo Bekele Gerba and Obbo Olbana Lelisa, were thrown into prison by the TPLF regime, which has militarily occupied Oromiyaa since 1991.who were recently sentenced  to lengthy prison term, are now transferred from Kality to the malaria infested Ziway prison. Zway already hosts some 3000 Oromo political prisoners. It is to be recalled that the renown Oromo singer Usmayyo Mussa fell sick while at this prison and passed away few months after being released


Two of the estimated 20,000 Oromo nationalist political prisoners in the Ethiopian empire, Obbo Bekele Gerba was the deputy Chairman of the opposition Oromo Federalist Democratic Movement (OFDM), and Obbo Olbana Lelisa a leader in the Oromo People’s Congress party (OPC) at the time of their arrestsFor the last 21 years Oromo political leaders and activists were killed ,disappeared , imprisoned and fled the country. All were and are accused by the Late   Meles  Zenawi’s regime of either supporting or being member of the OLF . Especially since 2004 -2011 in which the Oromo opposition political parties namely the Oromo federalist Democratic movement (OFDM) and the Oromo peoples congress ( OPC) won considerable seats in the parliament the imprisonment and torturing of the Oromo political leaders and activists are tripled. None of those imprisoned and suffered in the brutal hands of the Late    Meles Zenawi’s federal police and security agents were/ and are nothing to do with the OLF. They were /are members or leaders of the above mentioned legally formed political parties.These opposition parties fight the regime neck to neck exposed the authoritarian regime of Meles Zenawi. These genuine Oromo parties exposed the regime’s gross human right violations to the world community and drew the attention of the international human right organisations to follow and report the regime’s anti-peace and democracy. They are reporting the Meles Zenawi’s regime is responsible for the killings and imprisonment of dissents. As far as the name OLF exists and those opposition political parties and the Oromo people continue there resistance the wayane regime do not stop persecuting the Oromo nationals. So, to bring to the end the wayane persecution, all Oromo nationals must join and support the Mari biyyaa movement. Marii biyyaa is the only solution to bring our nations dream into reality. The dream of Mirga ofin of bulchu, the dream of aangoo siyaasa biyyatti harkatti galfachu. Political power is the determining factor for bilisummaa Oromo.

ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ በመላው አውሮፓ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ


ማጥራት፣ከቤት ንብረት ማፈናቀል፣ በሙስሊሙም፣ በክርስቲያኑም እየተደረገ ያለውን የሃይማኖት ጣልቃገብነትና ግረፋት፣ እስራት፣ ዛቻና ግድያ አንዲሁም በልማት ስም አየተፈጸመ ያለውን ገደብ ያጣ የመሪት ሽያጭና ስጦታ፣ እየፈጸመ ያለውን ህዝባዊና ሃገራዊ ክህደት ለመቃወምና ለማጋለጥ፣ ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ስልፍ ጁን 19/2013 ከ13:00 ስዓት ጀምሮ በቤልጄም ብራስልስ ሹማን ቁርጥ ቀጠሮ ይዘናል።
እየተፈጸመ ያለውን የዜጎችን መብት ረገጣ፣ የዘር መድሎ እንዲሁም ወያኔያዊ የሃገር ማጥፋት ውል ፍልስፍና በመቃወም! ለሃገረዎ ለወገኖዎ ያለዎትን ክብርና ሃገራዊ ስሜት በዚህ ደማቅ ሰልፍ ላይ በመገኘት ስሜትዎን በግንባር እንዲገልጹ ጥሪያችንን እናቀርባለን!
ከተለያዩ አውሮፓ ሀገራት ለምትመጡ በሃገር ኣቋራጭ አውቶብስ ለመጓጓዝ በድህረ-ገጹ ወይም ማስታወቂያው ላይ ያለውን ስልክ በመደወል ድምጽዎትን በፊት ለፊት ለማሰማት በአካባቢዎ ይደራጁ።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ለበለጠ መረጃ:-
Geneva፡
41223454206, 0041799483736
Belgium፡
0032493499619, 0032493284107, 0032493567554, 0032477327090,
German፡
004917647598748 004915211790603 00492217901605
Sweden፡
004673759578
Italy፡
0039690230273
Norway፡
004745206390

004747163809

Monday, May 20, 2013

ከሙስናው በስተጀርባ

ከኢየሩሳሌም አርአያ
በሕወሐት የተፈጠረው የቀውስ ማእበል አድማሱን እየለጠጠ መሔዱን ተከትሎ «ታማኝ» ሆነው በሙስና ሲያገለግሉ የቆዩትን ጭምር እየበላ እንደሚገኝ የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። በቀዳሚነት የሚያነሱት በጉምሩክ ቁልፍ ስልጣን የነበረውን የሕወሐት አባል ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ሲሆን እንዴትና በማን ወደስልጣን እንደመጣ እንዲሁም ምን-ምን ተግባራት ይፈፅምና ያስፈፅም እንደነበረ ምንጮቹ ሂደቱን እንደሚከተለው ይገልፁታል።
ገ/ዋህድ በ1993ዓ.ም ፓርቲው ለሁለት መሰንጠቁን ተከትሎ ወደ ስልጣን እንዲመጣ ተደረገ። ከጉምሩክ ሃላፊነት በተጨማሪ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተርነት ስልጣን እንዲጨብጥ የተደረገው በአቶ መለስ በተለይ በአዜብ ይሁንታ ጭምር እንደነበረ ምንጮቹ ይጠቁማሉ። ገ/ዋህድ ለዚህ ስልጣን የበቃው ለአቶ መለስ ቡድን በከፈለው መስዋእትነት ሲሆን በክፍፍሉ ማግስት የሙስና ዘመቻ ተከፍቶ እነአባተ ኪሾና ሌሎች እስር ቤት እንዲገቡ ቀጥተኛ ትእዛዝ ከመስጠት አንስቶ ራሱ ክስ አዘጋጅ፣ምስክርና ፈራጅ..በመሆን የላቀ ሚና መጫወቱን ያስታውሳሉ። በዚህ ተግባሩ የበለጠ ታማኝነቱን በማሳየቱ ከአዜብ በሚሰጠው ቀጥታ ትእዛዝ ሙስናውን ማከናወን መቀጠሉን ምንጮቹ አያያዘው ይጠቁማሉ። በ10ሺህ ቶን የሚገመት ቡና ከአዜብ በተቀበለው ትእዛዝ በህገወጥ መንገድ ከአገር ተዘርፎ የተሸጠበትና ጉዳዩም በፓርላማ ተነስቶ በጠ/ሚ/ሩ «የሌቦቹን እጅ እንቆርጣለን» የሚል አስቂኝ ምላሽ መሰጠቱን ያስታውሳሉ። በተጨማሪ በጉምሩክ ለረጅም አመት በመምሪያ ሃላፊነት ሽፋን የተቀመጠውና የቢሮውን የበላይ ሃላፊዎች በጥብቅ ከመቆጣጠር ጀምሮ እያንዳንዱን የሙስና ተግባር ከጀርባ ሆኖ የሚያስፈፅመው የአዜብ የቅርብ ስጋ ዘመድ ፍትሃነገስት ክንደያ እንደሚጠቀስና ግለሰቡ ቀረጥ ያልተከፈለባቸው 500 ሳተላይት ዲሾች እንዲገቡና በአዜብ በበላይነት ይመራ ለነበረው የዘረፋ ቡድን ለሰባት አመታት በየወሩ 20ሚሊዮን ከቴሌ በህገወጥ መንገድ እንዲዘረፍ ያደረገና በኋላም ከነገ/ዋህድ ጋር ሆኖ በርካታ ሙስናዎችን በዋናነት በማስፈፀም እንደሚጠቀስ ያመለክታሉ።
በሌላም በኩል የገ/ዋህድ ባለቤት ኰ/ል ሃይማኖት ስትጠቀስ ከሕወሐት አንጋፋ ሴት ታጋዮች አንዷ ናት፤ ከጡረታ ጋር በተያያዘ ከመከላከያ በመልቀቅ በአዜብ የበላይነት በሚመራው የሴቶች እና ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ቢሮ መስራት ቀጠለች። ለዚህ ቢሮ ከአሜሪካ መንግስት ብቻ በአመት እስከ 240ሚሊዮን ዶላር ይለገሳል። ገንዘቡ ለሚመለከታቸው ወገኖች ሳይሆን የሚውለው የነአዜብ ኪስ ማደለቢያ ሆኖ እንደሚዘረፍ ያመለከቱት ምንጮች ይህም ጉዳይ በፓርላማ ለቀድሞ ጠ/ሚ/ር ተነስቶ « ከእንግዲህ ቁጥጥር እናደርጋለን» የሚል የተድበሰበሰ ምላሽ እንድተሰጠ ያስታውሳሉ። ባልና ሚስቱን በተለያየ ወጥመድ በማስገባት የሙስና ጋሻ-ጃግሬ አድርገው የቆዩት አዜብ እንዲሁም ሌሎቹ ቱባ ባለስልጣናት መጠነ-ሰፊ ዘረፋና ሙስና ጉዳይ ሳይነካ ግልገሎቹን ብቻ (ያውም በአስፈፃሚነት ራሳቸው የመደቧቸውን) ተጠያቂ ማድረግ ተራ ድራማ ነው ሲሉ ምንጮቹ ያጣጥሉታል። በማስረጃነትም፥ 400 ሚሊዮን ብር ለ«ራዲሰን ሆቴል ግንባታ» በሚል ሽፋን በመፍቀድ 150ሚሊዮን ኪሳቸው ከከተቱትና በርካታ ብድሮችን በመፍቀድ (የስጋ ዘመዶቻቸውን ደላላ በማድረግ…) በሙስና የደለቡት አባይ ፀሃዬ ጨምሮ፣ የበታች ሙሰኞች ላይ <ምስክር> ሆነው የቀረቡትና ከአዜብ ጋር በሙስና የሰከሩት አባዱላ ገመዳ፣ የተለያዩ ድርጅቶች ባለቤት ስብሃት ነጋ፣ የቱጃሩን የቢሊዮን ብድር በግል ከመፍቀድ አንስቶ የታዋቂ ባለሃብቶች <ቀኝ እጅ> የሆኑትና ሚስታቸውን ጭምር በሙስና ያሰማሩት በረከት ስምኦን፣ ሶፍያን አህመድ፣ እንዲሁም ቪላዎችን ከ8 እስከ 10 ሚሊዮን ብር ወጪ በማስገንባትና በማከራየት የአገር ሃብት የሚዘርፉ ሁሉም የገዢው ትላልቅ ባለስልጣናት የሙስና ጉዳይ በዋቢነት ይጠቅሳሉ። ባጠቃላይ የስርአቱ ቁንጮዎች የሚያናቁራቸው የገዛ ጥቅምን ከማስጠበቅና አንዱ ጎራ ከሌላው በልጦ በሙስና የሚከብርበትን መንገድ ለማመቻቸት ብሎም ሌላኛውን በመጨፍለቅ ስልጣኑን ከነታማኝ ተከታዮቹ አስጠብቆ የሚቀጥልበትን ብቻ እንደሚያልም የጠቆሙት ምንጮቹ፣ ስርአቱ የአስተዳደር፣የፖለቲካ፣ የፖሊሲ…ወዘተ ልዩነት እንደሌለበት ያሰምሩበታል።

Sunday, May 12, 2013

የኦነግ ወታደሮች አንድ የጸጥታ ሹም ገድለው 7 ፖሊሶችን አቆሰሉ !

የኦነግ ወታደሮች አንድ የጸጥታ ሹም ገድለው 7 ፖሊሶችን አቆሰሉ
ግንቦት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም


በቦረና ዞን ፣ የሚኦ ወረዳ የጸጥታ ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት አቶ ጁኬ የአካባቢውን ፖሊሶች በማሰልፍ የኦነግን ታጣቂዎች ለማደን ሚያዚያ 29፣ 2005 ዓም ቢንቀሳቀሱም የኦነግ ወታደሮች ጨሶ እና ሜጢ በሚባል ቦታ ላይ አድፍጠው በመጠበቅ በወሰዱት እርምጃ ፣ የጸጥታ ሹሙን አቶ ጁኬን ገድለው፣ 7 ፖሊሶች ደግሞ አቁስለዋል። 6ቱ ፖሊሶች በያቤሎ ሆስፒታል ተኝተው በመታከም ላይ ሲሆኑ አንዱ ፖሊስ ደግሞ በጽኑ በመቁሰሉ ወደ አዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ተወስዷል ። የክልሉ የጸጥታ ዘርፍ ሹም የቀብር ስነስርአትም ግንቦት 1 ፣ 2005 ዓም በኢዲሎላ ከተማ መፈጸሙን የአካባቢው ወኪላችን ገልጿል።






ኢሳት ዜና


Thursday, May 9, 2013

150,000 Oromo people Displaced From Their Homes In Harerghe,Oromiya

150,000 Oromo people Displaced From Their Homes In Harerghe,Oromiya After Special Force Sent In 11 Towns By TPLF Ruling Class To Rob & Kill Ethnic Oromo People .Eyewithness said the Special Force have tied to Ethiopia Govt & TPLF Ruling Class.This news aired on 5.3.2013 On ESAT Radio.bilisummaatv@gmail.com 2013 BilisummaaTV Oromia






ሰማያዊ ፓርቲ የአፍሪካ ኅብረት 50ኛ ዓመት በዓል ሲከበር ሰላማዊ ሠልፍ ለመጥራት መወሰኑን አስታወቀ


በኢትዮጵያ የሚፈጸሙ የተለያዩ የሰብዓዊ፣ ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶችና ሕገወጥ ድርጊቶች እንዲቆሙ ለመንግሥት በተለያዩ 
ጊዜያት ጥያቄዎችን ቢያቀርብም፣ ከመንግሥት በኩል ምንም ምላሽ ማግኘት ባለመቻሉ የአፍሪካ ኅብረት 50ኛ ዓመት በዓል በሚከበርበት ወቅት፣ ጥቁር ልብስ በመልበስ ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ መወሰኑን ሰማያዊ ፓርቲ አስታወቀ፡፡ 





ማክሰኞ ማለዳ በጽሕፈት ቤቱ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጠው ሰማያዊ ፓርቲ፣ ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም. በሚከበረው የአፍሪካ ኅብረት 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓልና በዓሉ ከሚከበርበት ሁለት ቀናት ቀደም ብሎ ከግንቦት 15 ቀን ጀምሮ ሕዝቡ ጥቁር ልብስ እንዲለብስ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡ “የአሜሪካ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ሁሉም የአፍሪካ መሪዎች፣ የሌሎች አገሮች መንግሥታትና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች በሚገኙበትና በሚሰበሰቡበት የአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ ፊት ለፊት ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም. ሰላማዊ ሠልፍ በማድረግ ድምፃችንን እናሰማለን፤” ያሉት የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበርና የምርጫ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ስለሺ በይሳ ናቸው፡፡ 
ኃላፊው እንዳብራሩት፣ ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ሥርዓት መስፈን የሚታገሉ ጋዜጠኞች፣ የፓለቲካ ፓርቲዎችና አባላትን በአሸባሪነት ስም ማሰቃየትን ፓርቲው ይቃወማል፡፡ መንግሥት የታሰሩትን እንዲፈታም ጠይቋል፡፡ ዜጎች ሕገ መንግሥታዊ መብቶቻቸው ተጥሷል፡፡ ከኖሩበት ቦታ በታጠቁ ኃይሎች እንዲፈናቀሉ ማድረግ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው፡፡ በመሆኑም ድርጊቱን የፈጸሙ ለፍርድ መቅረብ እንዳለባቸው ፓርቲው ሌላ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ 
መንግሥት በሃይማኖታችን ጣልቃ አይግባ ብለው የጠየቁ የእስልምና ዕምነት ተከታዮች ታስረዋል፡፡ በአሸባሪነት ወንጀልም ተከሰዋል፡፡ በእስር እንዲማቅቁና ሰብዓዊ መብታቸው እንዲጣስ መደረጉ እንዲቆም ፓርቲው መጠየቁን፣ መንግሥት የኑሮ ውድነትን፣ ሥራ አጥነትንና በሙስና የተዘፈቁ ሹማምንትን ፖሊሲ በማውጣት እንዲቆጣጠር ቢጠየቅም፣ ጥያቄዎቹን ከማንቋሸሽ፣ ከማጣጣልና ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ከማለፍ ውጪ ምንም ምላሽ አለመስጠቱን ገልጸዋል፡፡ 
በመሆኑም ሰማያዊ ፓርቲ የመግለጫ ፓርቲ ብቻ ሳይሆን፣ ሰላማዊ ትግል የሚፈቅደውንና በሕገ መንግሥቱ የተፈቀደውን ለማድረግ ጠንክሮ እየሠራ መሆኑን አቶ ስለሺ ተናግረዋል፡፡ 
ፓርቲው በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ መሆኑን፣ የሚቻለውን ሁሉ እያደረገና በሕዝብ ዘንድም ተቀባይነቱ እየጨመረ መምጣቱን የሚናገሩት ምክትል ሊቀመንበሩ፣ ከነባር ፓርቲዎች ባልተናነሰ እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ 
ፓርቲው በሐዋሳ፣ በምሥራቅ ጐጃም፣በ ሸካ፣ በጐንደርና በድሬዳዋ የዞን አስተባባሪዎች እንዳሉት የገለጹት አቶ ስለሺ፣ ከገንዘብ ጀምሮ ብዙ ችግሮች ቢኖርባቸውም፣ በአባሎቻቸው ላይ እየደረሰ ያለውን ተፅዕኖ በመቋቋም ጠንክረው እየሠሩ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ 
ከፍተኛ አመራሩም ሆነ የምክር ቤቱ አባላት እንደሚተማመኑና ከልባቸው እየታገሉ መሆኑን የገለጹት አቶ ስለሺ፣ አንዳንዶቹ በሌላ ፓርቲ ውስጥ የነበሩና አለመተማመን ያመጣው ጣጣ ሰለባ የነበሩ ስለሆኑ በደንብ እንደሚተዋወቁ በመግለጽ፣ እርስ በርሳቸው አንዱ አንዱን በመሰለል ለገዢው ፓርቲ መረጃ ያቀብላል ለሚለው አሉታ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ 
በሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ ሆነው ለገዢው ፓርቲ መረጃ የሚያቀብሉ እንዳሉና አልፎ አልፎም ተለጣፊ ፓርቲ እንደሆነ ስለሚነገረው ጉዳይ ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ስለሺ፣ “እዚህ አገር ተሰባስበህ ስትሠራ ስም ይሰጥሃል፡፡ ከቅንጅትና ከአንድነት ጋር ቢያያይዙን እውነት ነው፡፡ ከኢሕአዴግ ጋር ግን እንኳ በፖለቲካ ደረጃ የሥራም ግንኙነት የነበረው አባል የለንም፤” ብለዋል፡፡ 
የፓርቲ አባላት የፖለቲካ እንቅስቃሴ ገብቷቸው ሳይሆን የጥገኝነት መጠየቂያ ሰነድ ለማግኘት አባል እንደሚሆኑ፣ ለዚህም ማረጋገጫ በቅርቡ በአመራር ደረጃ የነበረ አባል መሰደዱን በሚመለከት ማብራሪያ የሰጡት አቶ ስለሺ፣ ‹‹አይኖርም ማለት አይቻልም›› ካሉ በኋላ፣ በቅርቡ ተሰዷል ስለተባለው አባላቸው ደግሞ ‹‹አባሉ ጌታቸው አርዓያ ይባላል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ መሥራችና ስሙንም የሰየመው እሱ ነበር፡፡ የሥራ አስፈጻሚና የምክር ቤት አባልም ነበር፡፡ ከሰባት ወራት በፊት ግን ማመልከቻ በማቅረብ ከአመራርነት ወርዶ በተራ አባልነት ቀጥሎ ነበር፤” ብለው፣ የፓርቲው አባል ከመሆኑ በተጨማሪ ፍትሕ ጋዜጣ ላይ ይሠራ ስለነበር ደኅንነቶች እየተከታተሉት እንደተቸገረ እንደነገራቸውና በኋላም ተሰዷል መባሉን እንደሰሙ ተናግረዋል፡፡ 

Monday, May 6, 2013

የኢትዮጵያው ፀረ-ሽብር ሕግ የፕሬስ ነፃነትን አውድሟል

የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት ሣይንስና ባህል ድርጅት፣ እንዲሁም ለነፃ ፕሬስ መከበር የቆሙ ሌሎች ድርጅቶች የዛሬውን ዓለምአቀፍ የፕሬስ ነፃነት ቀን ምክንያት በማድረግ የዓለም ጋዜጠኞች ደህንነት እንዲረጋገጥ ጥሪ አድርገዋል።
ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት - ሂዩማን ራይትስ ዋች በበኩሉ የዛሬውን የዓለም የነፃ ፕሬስ ቀን ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያን ፀረ-ሽብር ህግ በመተቸት መግለጫ አውጥቷል።

ኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ በአቶ አንዱዓለም አራጌና በሌሎች ተከሣሾች ላይ ያፀናውን ፍርድ በመቃወም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት መግለጫ አውጥቷል፡፡


“የኢትዮጵያው ፀረ-ሽብር ሕግ የፕሬስ ነፃነትን አውድሟል” ይላል ለሰብዓዊ መብቶች መከበር የሚሟገተው መንግሥታዊ ያልሆነ ነፃ ድርጅት ሂዩማን ራይትስ ዋች ያወጣው መግለጫ ርዕስ፡፡

በናይሮቢ-ኬንያ የድርጅቱ ጥናት አቅራቢ ለቲሺያ ቤደር መግለጫውን ሲያብራሩ “ዓለም የፕሬስ ነፃነትን አክብሮ በሚውልበት በዛሬው ቀን ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ጋዜጠኞች ታስረው እንደሚገኙና አንዳንዶቹም በአገሪቱ ፀረ-ሽብር ሕግ የተፈረደባቸው እንደሆኑ ይህ ሕግም ከረቂቁ ጀምሮ ፀድቆ ሕግ እስከሆነበት ጊዜ ድረስ አሳሳቢ መሆኑንና የመናገር መብትን የሚያፍን መሆኑን ነው የገለፅነው።” ብለዋል፡፡

ሂዩማን ራይትስ ዋች እአአ ከ2011 ጀምሮ አሥራ አንድ ጋዜጠኞች /ስድስቱ በሌሉበት/ አፋኝ ባለው ፀረ-ሽብር ህግ ተከስሰው እንደተፈረደባቸው ይገልፃል።


በአሁኑ ወቅት በፀረ ሽብር ሕጉ የተከሰሱና ተፈርዶባቸው እሥር ቤት የሚገኙ ጋዜጠኞች በአጠቃላይ አምስት መሆናቸውን፤ እነርሱም እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ እና ውብሸት ታየ፣ እንዲሁም በፀረ-ሽብር ሕጉ ተከስሰው ፍርድ የሚጠባበቁ ሁለት ደግሞ ዩሱፍ ጌታቸውና ሰሎሞን ከበደ መሆናቸውን ለቲሺያ ቤደር ጠቅሰው የኢትዮጵያ መንግሥት የታሠሩትን በፍጥነት ከእሥር እንዲፈታ ጠይቀዋል።

“እአአ በ2009 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፀረ-ሽብር ሕግ ከፀደቀ ወዲህ ነፃ መገናኛ ብዙኃንን አሳብቦ ለማሳደድ በያዘው ሕግ የኢትዮጵያ ነፃ ጋዜጦች ተንኮታኩተዋል” ይላል የሂዩማን ራይትስ ዋች መግለጫ፡፡

መንግሥት ሆን ብሎ ጋዜጠኞች እንዳያሣትሙ እንደሚያደርግ፣ በኢንተርኔት የሚተቹትን ጽሁፎች እንደሚጋርድ፤ የማስተዋል አሣታሚ ባለቤት የሆነውን ማስተዋል ብርሃኑን እና የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረውን ተመስገን ደሣለኝን በዚሁ ፀረ-ሽብር ሕግ ከስሦ እንደሚያጉላላ ገልጿል።

የኢትዮጵያ መንግሥት እንደ ሂዩማን ራይትስ ዋች እና የጋዜጠኞች ደህንነት ተሟጋቹ ኮሚቴ - ሲፒጄ ያሉ ድርጅቶች የሚሠነዝሩበትን የመብት ጥሰት ነቀፋ አይቀበልም።

ባለሥልጣናቱ “ኔኦ-ሊብራልና የምዕራቡን የነፃነት ፍልስፍና ለማስፋፋት የሚሠሩ” ሲሉ ይተቿቸዋል፡፡ የአሁኑ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማሪያም ደሣለኝ በአንድ ወቅት ስለሰብዓዊ መብቶችና የመናገር ነፃነት በአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጋዜጠኛ ተጠይቀው “እኛ የምንከተለው የቻይናን ልማታዊ ዴሞክራሲ እንጂ የምዕራቡን ፍልስፍና አይደለም” ማለታቸውን ለሂዩማን ራይትስዋ አጥኚ አንስቼ ነበር።

“ጥሪአችን ስለ ርዕዮተ-ዓለም አይደለም በዓለም አቀፍ ደረጃ ሰለተደነገጉት የሰው ልጆች መብቶች እንጂ” ይላሉ ለቲሺያ ቤደር …
የሂዩማን ራይትስ ዋች የአፍሪካ ፕሮግራም ዳይሬክተርና የኢትዮጵያና የኤርትራ ጉዳዮች ኃላፊ ሌስሊ ሌፍኮ በበኩላቸው እአአ በ2007 ዓ.ም ኢትዮጵያ እሥር ቤት ውስጥ የሚገኙ ሁለት የኤርትራ ጋዜጠኞች ሳላህ ኢዲሪስ ጃማ እና ተስፋልደት ኪዳኔ ተስፋዝጊ ደህንነት ድርጅታቸውን እንደሚያሳስብ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት የእነዚህን ሁለት ጋዜጠኞች በጠበቃ የመወከል መብታቸውን እንዲያከብር፣ እንደ ዓለምአቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ባሉ ነፃ አካላት እንዲጎበኙ፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ በሕይወት መኖራቸውን እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል።

Thursday, May 2, 2013

Breaking News: TPLF sentenced Eskinder Nega and Andualem Arage








Ethiopia confirms jail for blogger, opposition figure
* Ethiopia has one of the most restricted media in the world and the highest number of journalists living in exile
An Ethiopian Kangaroo court on Thursday dismissed the appeal of blogger Eskinder Nega and opposition leader Andualem Arage who were jailed last year for terror-related offences.

"The sentencing is still correct so there is no reduction," said Supreme Court judge Dagne Melaku, confirming Eskinder's jail term of 18 years and Andualem's life sentence.

One of the charges -- serving as a leader of a terrorist organisation -- was dropped, but had no affect on sentencing. After the ruling, Eskinder made an emotional appeal to the court which was crowded with family, friends and diplomats. "The truth will set us free," he said. "We want the Ethiopian public to know that the truth will reveal itself, it's only a matter of time."

Both men are accused of links to the outlawed opposition group Ginbot 7. "The walls of justice will be demolished," Andualem told . Four other men also jailed for terror-related charges had their appeal quashed.

One other defendant, however, Kinfe Michael, had his sentence reduced from 25 years to 16 years. Rights groups have called Ethiopia's anti-terrorism legislation vague and accuse the government of using the law to stifle peaceful dissent.

"I am very sad, I am very angry, I cannot talk rationally," Eskinder's wife Serkalem Fasil told   after the decision.

Defence lawyer Abebe Guta said that justice had not been served, and that if his clients agreed, they would appeal to court of cassation, Ethiopia's highest court. Ethiopia has one of the most restricted media in the world and the highest number of journalists living in exile, according to US-based press watchdog, the Committee to Protect Journalists.

Last year Eskinder was awarded the prestigious PEN America's "Freedom to Write" annual prize. Rights groups including Amnesty International and Human Rights Watch condemned the initial conviction of the Eskinder in July 2012.