Thursday, February 28, 2013

Oromo Students expelled not one Tigray

Oromo studenst have been suspended and expelled from Addiss Abab University but not one Tigray or Amhara that were involved.

They were expelled and suspended for a riot that took place based on a deragotry insult written on a wall against Oromos. The writers of dergatory are Tigrays. The riot included Tigrays, Amahras and Oromos. But Oromos were singled out and expelled and and suspended. Not one Tigray was reprimanded or expelled.



Friday, February 22, 2013

መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ ይመነጫል

መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ ይመነጫል?

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ-ማርያም 


የካቲት 2005


በአለፉት ሠላሳ አምስት ዓመታት ኢትዮጵያ ችግሮችን መፈልፈያ መሣሪያ ሆናለች፤ ለብዙ ምዕተ-ዓመታት ይዘናቸው (ምናልባትም አቅፈናቸው ማለት ይሻል ይሆናል) ስንንከባለል የቆዩ ችግሮች ሞልተውናል፤ እያሰብን እነዚያን የቆዩ ችግሮቻችንን በመፍታት ፋንታ ሌሎች አዳዲስ ችግሮችን እየፈለፈልን የተቆላለፉና የተወሳሰቡ፣ ውላቸው የጠፋ ችግሮችን ፈጥረናል፤ እየፈጠርንም ነው፤ አሁን በመፈጠር ላይ ያለው አዲስ ችግር እስላማዊ መንግሥት በኢትዮጵያ የሚል ነው፤ እስቲ እንመልከተው፡፡


በሩቁ እንጀምር፤ እስላማዊ መንግሥታት ያቋቋሙ አገሮች አሉ፤ አንዳቸውም ሰላም የላቸውም፤ እስላማዊ ቡድኖች በምርጫ አሸንፈው ሥልጣን የያዙ አሉ፤ ለምሳሌ በቅርቡ በአረብ አገሮች በተጀመረው የፖሊቲካ እድገት ለውጥ በቱኒስያና በግብጽ እስላማዊ ቡድኖች አሸንፈው ሥልጣን ይዘዋል፤ በዚህም ምክንያት በቱኒስያና በግብጽ የለውጥ ጥያቄ አገርሽቶ አንደገና ሰዎች እየሞቱ ነው፤ በነዚህና በሌሎችም አገሮች የሚገኙት ወጣቶች የሚፈልጉት የሰው ልጆች ሁሉ መብቶች የሚከበሩባቸውና በሙሉ የግለሰብ ነጻነት የተረጋገጡባቸው አገሮች እንዲኖራቸውና በእኩልነት ኩሩ ዜጎች ሆነው እንዲኖሩ ነው፤ የአንድ አገር ዜጎች የተለያየ ዘር፣ የተለያየ የቆዳ ቀለም፣ የተለያየ ቁመትና ውፍረት፣ የተለያየ ጾታና ዕድሜ፣ የተለያየ ቋንቋ፣ የተለያየ ሃይማኖት፣ የተለያየ የፖሊቲካ አመለካከት፣ የተለያየ ትምህርት፣ የተለያየ ሙያና የተለያየ ገቢ ሊኖራቸው ይችላል፤ የጋራ ማንነታቸው ዜግነት ነው፤ እኩልነታቸው በዜግነታቸው ነው፤ አንድነታቸው በዜግነታቸው ነው፤ እኩልነታቸውንና አንድነታቸውን የሚያረጋግጥላቸውና ሚዛኑን የሚጠብቅላቸው ከበላይ ሆኖ ሁሉንም የሚገዛው ሕግ ነው፡በቡድን ወይም በጅምላ የሚያስቡ ሰዎች የሕግን ባሕርይ አያውቁትም፤ ‹‹ክርስቲያኖች እስላሞችን እንጨርሳለን›› አሉ፤ ወይም እስላሞች ክርስቲያኖችን እንጨርሳለን›› አሉ፤ በሚል አሉባልታ ላይ ክስ ተመሥርቶ ሕጋዊ ፍርድ መጠበቅ አይቻልም፤ በየትም ሆነ በማንኛውም ጊዜ ጽንፈኛ እምነትና አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎች ይገኛሉ፤ እነዚህ ግለሰቦች ሕልማቸውንም ሆነ ቅዠታቸውን በስውርም ሆነ በአደባባይ ይገልጻሉ፤ ለምሳሌ በአሜሪካ ጥቁሮችንና ይሁዲዎችን ከአገሩ ጠራርገን እናወጣና ንጹሕ የነጮች አገር እንፈጥራለን የሚሉ ግለሰቦች አሉ፤ ይህ እምነት ለአሜሪካ ማኅበረሰብ መርዝ ነው፤ አሜሪካ የነጻነት አገር ነው፤ የነጭ ዘረኞቹ መርዛቸውን ለመንዛት መብት አላቸው፤ የዘረኞቹን መብት ለማፈን የሚወሰድ የጡንቻ እርምጃ ሁሉ አሜሪካ የነጻነት አገር መሆኑን ይሽራል፤ ከዚያም በላይ የአሜሪካ መንግሥት በሚከተለው ዘዴ ከነጭ ዘረኞቹ የተሻለ አይሆንም ነበር፤ ስለዚህም ነጭ ዘረኞችን ለመቋቋም የሚወሰደው አርምጃ አሜሪካ የነጻነት አገር መሆኑን ሳይሽርና ነጭ ዘረኞቹም እምነታቸውን የመግለጽ መብታቸው ሳይደፈጠጥ መሆን አለበት፤ የነጻነት ትርጉሙ ይህ ብቻ ነው፡፡


በሥልጣን ወንበር ላይ ስለተቀመጡ ብቻ አንድ ዓይነት የፖሊቲካ እምነት ብቻ ይዞ ሌላውን መደፍጠጥ፣ መንግሥት የባረከውን አንድ ዓይነት የኦርቶዶከስ ሃይማኖት ብቻ ማደርጀትና ሌላውን ማፈን፣ መንግሥት የባረከውን አንድ ዓይነት የእስልምና ሃይማኖት ብቻ ማደርጀትና ሌላውን ማፈን ልማድና የአሠራር ባህል እየሆነ ሲሄድ ሁሉንም ነገር አንድ ዓይነት ብቻ ለማድረግ የሚታየው ጥረት የኢትዮጵያን ጉራማይሌ ባሕርይ የሚቃረን በመሆኑ ስር አይኖረውም፤ ይህ ሁሉም ሰው ሊያስብበት የሚገባው አንዱ ነገር ነው፤ ሁለተኛው አንድ ወይም ጥቂት ሰዎች በኢትዮጵያ ውስጥ እስላማዊ መንግሥት እናቋቁማለን ቢሉ አገር የሚሸበርበት ምንም ምክንያት የለም፤ ኢትዮጵያን የኦርቶዶክስ ክርስቲያን አገር ለማድረግ የሚመኙም አሉ፤ ኢትዮጵያን ሃይማኖት-አልባ የጉግማንጉግ አገር ለማድረግ የሚፈልጉ አሉ፤ ኢትዮጵያ በአንድ አጋጣሚ ወንበሩ ላይ የወጣ ጉልበተኛ የሚያትምባትን እምነትም ሆነ ሃይማኖት የማትቀበል አገር መሆንዋ ተደጋግሞ የታየ ነው፤ ኢትዮጵያን የይሁዲ አገር ለማድረግ ተሞክሮአል፤ ኢትዮጵያን የክርስቲያን አገር ለማድረግም ተሞክሮአል፤ ኢትዮጵያን የእስላም አገር ለማድረግም ተሞክሮአል፤ ሁሉም አልሆነም፤ ኢትዮጵያ የሁሉም አገር ሆና ዘልቃለች፤ ይህንን በማክሸፍ ለማንም ምንም ጥቅም አይገኝም፤ በአንጻሩ ደግሞ የሥልጣን ወንበሩ ላይ የወጡ ጉልበተኞች ሁሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ በጉጉት የሚጠብቀውን የነጻነት ጮራ እያዳፈኑ የነጻነትን፣ የእኩልነትንና የሕግ የበላይነትን ዓላማ ለማክሸፍ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እየቀጠለ ነው፡፡


የነጻነትና የሕጋዊነት መክሸፍ የሰላም ጠንቅ ነው፤ የሰላም መክሸፍ የልማት ጠንቅ ነው፤ የልማት መክሸፍ ደሀነት ነው፤ ደሀነት የሞት አፋፍ ነው፤ ይህንን ለመገንዘብ የሚያዳግተው ሃያ አንድ ዓመት የሞላው ሰው አለ? ኢትዮጵያን ለመምራት የሚደናበሩት ሰዎች ሁሉ ሃያ አንድ ዓመት አልፎአቸዋል፤ ነገር ግን ከላይ የተገለጸው የመክሸፍ ጉዞ ጭራሽ አይታያቸውም፤የሚታየውም ሲነግራቸው የተበለጡ ስለሚመስላቸው አይሰሙትም፤ ስለዚህም የሚታየውን ሳያዩ፣ የሚሰማውን ሳይሰሙ ጊዜ የሚበላውን ጉልበታቸውን ብቻ ተማምነው በጭፍን እንምራችሁ የሚሉትን ተከትለን ለእኛ በሚታየንና ለእነሱ በተሰወረባቸው ገደል ውስጥ ለምን አብረን እንግባ? አብረን ገደል በመግባት አንድነታችንን የምንጠብቅ የሚመስላቸው ሰዎች በሁለት በኩል ይሳሳታሉ፤ አንደኛ ከአገዛዙ መሪዎች ዘንድ የሎሌ ተከታይነትን እንጂ የአኩልነት አንድነትን አያገኙም፤ እኩልነት በሌለበት አንድነት አይፈጠርም፤ ሁለተኛ ወደገደል የሚጨምር አንድነትን መምረጥ ሕይወትን ትቶ ሞትን መምረጥ ነው፡፡


በሃያ አንድ ዓመት ውስጥ መክተፍ-መከታተፍ ሙያ ሆነ፤ ብዙ ሰዎችና ድርጅቶች ሠለጠኑበት፤ መክተፍ-መከታተፍ አብሮ የመኖር ጸር ነው፤ አብሮ የመኖር ጸር የሚሆነው በፍቅር ፋንታ ጥላቻን፣ በሰላም ፋንታ ጠብን፣ በመረዳዳት ፋንታ መጋጨትን፣ በልማት ፋንታ ጦርነትን በመንዛት ነው፤ አንዳንድ ቋንቋ ተናጋሪዎችን በግልጽም ሆነ በስውር እንደጠላት መቁጠርና በእነሱ ላይ ቂምን እንዲቋጥሩ ማድረጉ የማንንም የፖሊቲካ ቡድን፣ የኢትዮጵያን ሕዝብም ይጎዳል እንጂ አይረዳም፡፡

አሁን ደግሞ በአንድ በኩል በኦርቶዶክስ ሃይማኖት ላይ በየገዳማቱና ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃትና በሊቀ ጳጳሳት ምርጫው ላይ አገዛዙ እያሳየ ያለው ጣልቃ-ገብነት የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮችን እያስቀየመና እያስኮረፈ ነው፤ በሌላ በኩል በእስልምና ሃይማኖት ላይም የሚታየውን ጣልቃ-ገብነት ተከታዮቹ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ በርትተው በመቋቋማቸው እየደረሰባቸው ያለው ግፍ ለጆሮ እየቀፈፈና በጣም አሳፋሪ እየሆነ ነው፡፡
ይህ በሃይማኖቶች ላይ የተጀመረው ዘመቻ ውጤት ይኖረዋል፤ ውጤቱ በአገዛዙ የውስጥም ሆነ የውጭ አመራሩ ላይ ከባድ ተጽእኖ ይኖረዋል፤ የሃይማኖቶቹ ጉዳይ እንደጎሣዎች መከታተፍ በኑሮ ላይ ብቻ ጫናውን የሚያሳርፍና በምድር የሚንከላወስ አይደለም፤ ወደሰማይ ያርጋል፤ የሰማይ ሠራዊትን ይጠራል፤ ያንን ኃይል እንኳን የኢትዮጵያ የጦር ኃይልና የአሜሪካውም አይችለውም፤ ዓይን ያለው ያያል፤ ጆሮ ያለው ይሰማል፤ ልብ ያለው ያስተውላል፤ ዶላር ነፍስን አይገዛም፤ ክብርን አይገዛም፤ ወዳጅንም አይገዛም፡፡

Wednesday, February 20, 2013


ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ልዩ አካባቢዎች “በሙስሊሙ ማኅበረሰብ አባላት ላይ ያነጣጠረ የቤት ለቤት ፍተሻና ዘረፋ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ -የቤት ለቤት ፍተሻና ዘረፋ እየተካሄደ ነው   ዘገባውን ያዳምጡት

Friday, February 8, 2013

Charges renewed against Ethiopian journalist Temesghen


Charges renewed against Ethiopian journalist Temesghen




A court revived criminal charges against Temesghen Desalegn today. (CPJ
Nairobi, February 8, 2013--The Committee to Protect Journalists condemns the revival of criminal charges against Ethiopian journalist Temesghen Desalegn today in what appears to be a politicized court hearing designed to censor one of the few critical voices left in the country.
A judge in the Federal High Court in the capital, Addis Ababa, revived three charges against Temesghen, former chief editor of the now-defunct Feteh, and one against the general manager of Mastewal Publishing, the publishing company that formerly printedFeteh, according to local journalists who attended the hearing. Temesghen faces charges of "outrages against the constitution," defaming the government, and false publication of articles, while the manager of Mastewal Publishing faces an unspecified charge for allowing the weekly to be published. Under Ethiopian law, a printing company is also held accountable for a press offense by a publication that it publishes.
The charges were filed in connection with articles published in Feteh before the death of Prime Minister Meles Zenawi in August 2012, according to CPJ's review of the charge sheet. State prosecutors cited Feteh articles in court that they said falsely accused the government of interfering in religious affairs and discrimination against certain ethnic groups, as well as articles that allegedly incited violence.
The next court date is scheduled for March 26, local journalists told CPJ.
State prosecutors had suspended the charges against Temesghen in August without explanation, but announced on December 12 that they would re-file unspecified charges against him, Temesghen told CPJ. The court date was adjourned until today, when Temesghen learned he faced the same charges as last year.
Shimeles Kemal, a government spokesman, told local journalists that the charges had been renewed based on further incriminating evidence. He did not offer details.
"Authorities have not provided any new evidence to support the revival of these charges," said CPJ East Africa Consultant Tom Rhodes. "This court case appears to be a political effort to stifle one of the few independent voices left in the country and ensure he cannot continue in the profession. All charges placed against Temesghen and his publisher must be dropped immediately."
Feteh has not published since July 2012, when the government ordered the printer not to publish it. The ministry had blocked the distribution of a Feteh edition that included a front-page story about the conflicting reports surrounding the illness of Meles, according to news reports.
Temesghen has been harassed by authorities in the past. In August 2012, he launched a new independent bimonthly, Addis Times, but the state-run Ethiopian Broadcast Authority suspended the publication in January and rejected its application for the renewal of a certificate necessary to hold a printing license, local journalists told CPJ. Authorities cited the Addis Times' failure to carry out administrative procedures including delivering copies to the national archive and publishing names of their shareholders, according to CPJ's review of the official statement. Temesghen denied the allegations, and said they were designed to prevent the paper from further publication.
At least seven journalists are behind bars in Ethiopia, making the country the second leading jailer of journalists in Africa, according to CPJ research. Independent bloggerEskinder Nega was sentenced on July 2012 to 18 years in prison on charges of participating in a terrorist organization and inciting anti-government protests, according to CPJ research.
Source <<<Committee to protect journalists   (CPJ)

Sunday, February 3, 2013

Human Rights Watch World Report 2013

Human Rights Watch World Report 2013 

Ethiopia

The sudden death in August 2012 of Ethiopia’s long-serving and powerful prime minister, Meles Zenawi, provoked uncertainty over the country’s political transition, both domestically and among Ethiopia’s international partners. Ethiopia’s human rights record has sharply deteriorated, especially over the past few years, and although a new prime minister, Hailemariam Desalegn, took office in September, it remains to be seen whether the government under his leadership will undertake human rights reforms.

Ethiopian authorities continued to severely restrict basic rights of freedom of expression, association, and assembly in 2012. Thirty journalists and opposition members were convicted under the country’s vague Anti-Terrorism Proclamation of 2009.The security forces responded to protests by the Muslim community in Oromia and Addis Ababa, the capital, with arbitrary arrests, detentions, and beatings.

The Ethiopian government continues to implement its “villagization” program: the resettlement of 1.5 million rural villagers in five regions of Ethiopia ostensibly to increase their access to basic services. Many villagers in Gambella region have been forcibly displaced, causing considerable hardship. The government is also forcibly displacing indigenous pastoral communities in Ethiopia’s Lower Omo Valley to make way for state-run sugar plantations.

Freedom of Expression, Association, and Assembly

Since the promulgation in 2009 of the Charities and Societies Proclamation (CSO Law), which regulates nongovernmental organizations, and the AntiTerrorism Proclamation, freedom of expression, assembly, and association have been increasingly restricted in Ethiopia. The effect of these two laws, coupled with the government’s widespread and persistent harassment, threats, and intimidation of civil society activists, journalists, and others who comment on sensitive issues or express views critical of government policy, has been severe. Ethiopia’s most important human rights groups have been compelled to dramatically scale-down operations or remove human rights activities from their man dates, and an unknown number of organizations have closed entirely. Several of the country’s most experienced and reputable human rights activists have fled the country due to threats. The environment is equally hostile for independent media: more journalists have fled Ethiopia than any other country in the world due to threats and intimidation in the last decade—at least 79, according to the Committee to Protect Journalists (CPJ).

The Anti-Terrorism Proclamation is being used to target perceived opponents, stifle dissent, and silence journalists. In 2012, 30 political activists, opposition party members, and journalists were convicted on vaguely defined terrorism offenses. Eleven journalists have been convicted under the law since 2011.

On January 26, a court in Addis Ababa sentenced both deputy editor Woubshet Taye and columnist Reeyot Alemu of the now-defunct weekly Awramaba Times to 14 years in prison. Reeyot’s sentence was later reduced to five years upon
appeal and most of the charges were dropped.

የመለስ ራዕይ በ‹‹አዲስ ታይምስ›› መፅሄት ተተገበረ!!!

የመለስ ራዕይ በ‹‹አዲስ ታይምስ›› መፅሄት ተተገበረ



          ምንም ጥርጥር የለውም መለስ ዜናዊ ፍፁም አምባገነን ነበር፡፡ ምንም ጥርጥር የለውም ከአንድ ክፍለ ጦር በላይ የተለየ ሀሳብን እና ነፃ ሚዲያን  ይፈራል፡፡ ምንም ጥርጥር የለውም ወራሾቹም ሀሳቡን በነፃነት የሚገልፅን ከመለስ በባሰ መልኩ ይፈራሉ፡፡ ይህ ፍራቻቸው ወደ ጭፍን አምባገነንነት ስለቀየራቸው መላ ሀገሪቷን ወደ ድቅድቅ ጨለማ እየገፏት ነው፡፡ 
የሆነ ሆኖ መለስ ከአደባባይ ከራቀ በኋላ በፍትህ ቤተሰቦች የሚመራ ትልቅ ሚዲያ ሲዘጋ ‹‹አዲስ ታይምስ›› ሁለተኛዋ ናት፡፡ 
ለ‹‹አዲስ ታይምስ›› መዘጋት መንግስት የሰጠው ሶስት ምክንያት፡-
1. የባለቤትነት ድርሻ ከአንዱ ወደ ሌላው ሲዞር በ15 ቀን ውስጥ አላሳወቃችሁም፣
2. ህትመቱ ሲወጣ ለቤተ-መዛግብት ሁለት ሁለት ኮፒ በነፃ አልሰጣችሁም እና
3. የገንዘብ ምንጫችሁ አይታወቅም የሚሉ ናቸው፡፡ 
በቃ፡፡ ህዝብን መናቅ ሙያ ብሎ የያዘው ገዥው ፓርቲ መፅሄታችንን ለመዝጋት የሰጠው ምክንያት እነዚህ ናቸው፡፡ አስገራሚው ጉዳይ የባለቤትነት ድርሻ ሲዞር በጊዜው ማስታወቃችን፣ ለቤተ-መዛግብትም ህትመታችን ሲወጣ ሁለት ሁለት ሳይሆን አምስት አምስት ኮፒ በነፃ የሰጠንበትን ማስረጃ ማቅረባችን እና ምንጩ አይታወቅም ለሚለው ደግሞ የመፅሄቱ ኮፒ 35 ሺህ በመሆኑ ምንጩ ህዝባችን (አንባቢያን) መሆናቸውን ብሮድ ካስት አብጠርጥሮ ማወቁ ነው፡፡ 
ይሁንና እነዚህ የተጠቀሱት ምክንያቶችስ ተፈፅመው ቢሆን እንኳ አዋጁ የሚለው አስራ አምስት ሺህ ብር ያስቀጣል ነው፡፡ ታዲያ መዝጋትን ከየት ያመጡት ህግ ነው? ማንአለብኝነት እና ጉልበተኝነት ካልሆነ በቀር፡፡
በነገራችን ላይ ‹‹ብሮድ ካስት›› በሚል ስያሜ የተመሰረተ ተቋም ከቴሌቪዥንና ራዲዮን ውጭ ያልተፈቀደለትን የ‹‹ህትመት ሚዲያ››ንም ጨምሮ መቆጣጠሩ ከበረከት ስምዖን ውጪ ለማንም ግልፅ አይደለም፡፡ ለቤተ-መፅሀፍት መፅሄት ማስገባትን እና አለማስገባትንም እንዲሁ ከሙያ ብቃት ጋር ያላቸውን ግንኙነት በረከት ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡ 
… አሁን የመለስ ራዕይ ግልፅ ነው፤ አፈናውን አጠናክሮ ማስቀጠል፡፡ 
መቼም ሃያ አንድ ዓመት ሙሉ በስልጣን ላይ ተቀምጦ ምንም ያልፈየደን መሪ፣ ልክ ስልጣን በያዘ ማግስት ህይወቱ እንዳለፈ ሰው ሁሉ ‹‹ራዕይ ነበረው፣ እናስቀጥለዋለን…›› ጂኒ ቁልቋል ማለቱ በህዝብ ላይ ማላገጥ ነው፡፡ ለሀገር የሚጠቅም ራዕይ ቢኖረው ኖሮ፣ በስልጣን ላይ ያሳለፋቸው ሃያ አንድ ዓመታት ከበቂ በላይ ነበሩና፡፡ 
ጥያቄው ግን ‹‹ይህ የቀልድ ዘመን ዕድሜው ስንት ነው?›› የሚል ነው፡፡ ስድስት ወር፣ አንድ ዓመት ወይስ ሁለት ዓመት? ….በጣም… በጣም በቅርቡ የምናየው ይሆናል፡፡ (በዓለም አቀፍ መድረክ የተሸነፈበትንም ታላቅ ዜና ጊዜው ሲደርስ እንሰማለን፡፡)
የመለስ ራዕይ በ‹‹አዲስ ታይምስ›› መፅሄት ተተገበረ!!!
ምንም ጥርጥር የለውም መለስ ዜናዊ ፍፁም አምባገነን ነበር፡፡ ምንም ጥርጥር የለውም ከአንድ ክፍለ ጦር በላይ የተለየ ሀሳብን እና ነፃ ሚዲያን ይፈራል፡፡ ምንም ጥርጥር የለውም ወራሾቹም ሀሳቡን በነፃነት የሚገልፅን ከመለስ በባሰ መልኩ ይፈራሉ፡፡ ይህ ፍራቻቸው ወደ ጭፍን አምባገነንነት ስለቀየራቸው መላ ሀገሪቷን ወደ ድቅድቅ ጨለማ እየገፏት ነው፡፡ 
የሆነ ሆኖ መለስ ከአደባባይ ከራቀ በኋላ በፍትህ ቤተሰቦች የሚመራ ትልቅ ሚዲያ ሲዘጋ ‹‹አዲስ ታይምስ›› ሁለተኛዋ ናት፡፡ 
ለ‹‹አዲስ ታይምስ›› መዘጋት መንግስት የሰጠው ሶስት ምክንያት፡-
1. የባለቤትነት ድርሻ ከአንዱ ወደ ሌላው ሲዞር በ15 ቀን ውስጥ አላሳወቃችሁም፣
2. ህትመቱ ሲወጣ ለቤተ-መዛግብት ሁለት ሁለት ኮፒ በነፃ አልሰጣችሁም እና
3. የገንዘብ ምንጫችሁ አይታወቅም የሚሉ ናቸው፡፡ 
በቃ፡፡ ህዝብን መናቅ ሙያ ብሎ የያዘው ገዥው ፓርቲ መፅሄታችንን ለመዝጋት የሰጠው ምክንያት እነዚህ ናቸው፡፡ አስገራሚው ጉዳይ የባለቤትነት ድርሻ ሲዞር በጊዜው ማስታወቃችን፣ ለቤተ-መዛግብትም ህትመታችን ሲወጣ ሁለት ሁለት ሳይሆን አምስት አምስት ኮፒ በነፃ የሰጠንበትን ማስረጃ ማቅረባችን እና ምንጩ አይታወቅም ለሚለው ደግሞ የመፅሄቱ ኮፒ 35 ሺህ በመሆኑ ምንጩ ህዝባችን (አንባቢያን) መሆናቸውን ብሮድ ካስት አብጠርጥሮ ማወቁ ነው፡፡ 
ይሁንና እነዚህ የተጠቀሱት ምክንያቶችስ ተፈፅመው ቢሆን እንኳ አዋጁ የሚለው አስራ አምስት ሺህ ብር ያስቀጣል ነው፡፡ ታዲያ መዝጋትን ከየት ያመጡት ህግ ነው? ማንአለብኝነት እና ጉልበተኝነት ካልሆነ በቀር፡፡
በነገራችን ላይ ‹‹ብሮድ ካስት›› በሚል ስያሜ የተመሰረተ ተቋም ከቴሌቪዥንና ራዲዮን ውጭ ያልተፈቀደለትን የ‹‹ህትመት ሚዲያ››ንም ጨምሮ መቆጣጠሩ ከበረከት ስምዖን ውጪ ለማንም ግልፅ አይደለም፡፡ ለቤተ-መፅሀፍት መፅሄት ማስገባትን እና አለማስገባትንም እንዲሁ ከሙያ ብቃት ጋር ያላቸውን ግንኙነት በረከት ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡ 
… አሁን የመለስ ራዕይ ግልፅ ነው፤ አፈናውን አጠናክሮ ማስቀጠል፡፡ 
መቼም ሃያ አንድ ዓመት ሙሉ በስልጣን ላይ ተቀምጦ ምንም ያልፈየደን መሪ፣ ልክ ስልጣን በያዘ ማግስት ህይወቱ እንዳለፈ ሰው ሁሉ ‹‹ራዕይ ነበረው፣ እናስቀጥለዋለን…›› ጂኒ ቁልቋል ማለቱ በህዝብ ላይ ማላገጥ ነው፡፡ ለሀገር የሚጠቅም ራዕይ ቢኖረው ኖሮ፣ በስልጣን ላይ ያሳለፋቸው ሃያ አንድ ዓመታት ከበቂ በላይ ነበሩና፡፡ 
ጥያቄው ግን ‹‹ይህ የቀልድ ዘመን ዕድሜው ስንት ነው?›› የሚል ነው፡፡ ስድስት ወር፣ አንድ ዓመት ወይስ ሁለት ዓመት? ….በጣም… በጣም በቅርቡ የምናየው ይሆናል፡፡ (በዓለም አቀፍ መድረክ የተሸነፈበትንም ታላቅ ዜና ጊዜው ሲደርስ እንሰማለን፡፡)