Monday, February 3, 2014

በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ጊቢ ውስጥ (ዩኒቨርሲቲ ወይሰ የጦር ካመፕ???


በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ጊቢ ውስጥ አስቸጋሪ ሁኔታዎች እየተከሰቱ እንደሆነ በአካባቢው የሚገኙ ያነጋገርናቸው ተማሪዎችና ነዋሪዎች አረጋግጠውልናል። ፌደራል ፓሊስና አድማ በታኝ ሁኔታውን ለማብረድ ሀይል ተጠቅሟል
በዛው ቀን ከሰዓት በኋላ 200 የሚጠጉ ተማሪዎች ታምመው ወደ ህክምና ተቋማት እንደሄዱና፣ 10 የሚሆኑት የጸና ህመም እንዳጋጠማቸው ጠቅሷል፡፡

ከክስተቱ ጋር በተያያዘ በርካታ የፖሊስ አባላት በዩኒቨርሲቲው ካምፓስ ውስጥ በብዛት እንደነበሩና የተጎዳ ተማሪ ግን እንደሌለ ተናግሯል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በዚህ ዓመት በሚያካሂደው የተማሪዎች የስፖርት ውድድር ሳቢያ ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ትኩረቱን ነፍጎናል፤ በመጸዳጃና በምግብ ቤት አካባቢ ችግር አለ ብሏል፡፡

ተማሪው፣ ከቀናት በፊት የዩኒቨርሲቲው የኢንጅነሪንግ ተማሪዎች ባነሱትና እስካሁንም ባልተመለሰው ጥያቄያቸው ሳቢያ ከፖሊስ ሀይሎች ጋር በተቀሰቀሰው ግጭት ሳቢያ ግን በርካታ ተማሪዎች የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ተናግሯል፡፡

No comments:

Post a Comment