Monday, June 9, 2014

ነቀምቴ ላይ አራት ከፍተኛ ሐኪሞች ታሥረዋል?

ዶ/ር አዳም ለማ፤ የቀዶ ሕክምና ሐኪም፣ ዶ/ር ኢሣያስ ብርሃኑና ዶ/ር በላይ ቤተማርያም የማኅፀንና የፅንስ ስፔሻሊስቶች፣ ዶ/ር ታመነ አበራ፤ ቀድሞ የሆስፒታሉ የሕክምና ዳይሬክተርና አሁን ለስፔሻላይዜሽን የጥቁር አንበሣ ሬዚደንት ሐኪም፣ እንዲሁም ዶ/ር ሪም ጆንግ ሆ፤ ኮርያዊ የአጥንት ሐኪም፡፡
ሁሉም በነቀምቴ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ አገልግለዋል፡፡

ዛሬ ኮርያዊው ሐኪም ከሥራ ሲሠናበቱ አራቱ ኢትዮጵያዊያን ግን በቁጥጥር ሥር ውለው ነቀምቴ በሚገኘው ማረሚያ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፡፡

የእነዚህ ለረዥም ዓመታት አገልግሎት ሰጥተዋል የሚባሉ ሐኪሞች ከሥራቸውና ከደመወዛቸው መታገድ፣ አልፎም መታሠር መነጋገሪያ እየሆነ ነው፡፡

“ጥፋታቸው” የተባለው ምን ይሆን? በአካባቢያቸው ያሉ ሰዎችስ “ጥፋተኛ ናቸው” ብለው ያምናሉ?

የተያያዘው ዘገባ የፖሊስን፣ የሆስፒታሉን አስተዳደር፣ የእሥረኞቹን ሐኪሞች ቤተሰቦችና ጠበቃ የሚሉትን ይዞ ዝርዝር መረጃ ይሰጥዎታል፡፡
ያዳምጡት፡

ቪኦኤ

http://amharic.voanews.com/content/nekempte-doctors-arrested/1635248.html 

ጥፋተኛ ናቸው” ብለው ያምናሉ? ????