Sunday, December 7, 2014

ኢትዮጵያ የኢንተርኔት መብት ከሌላቸው 10 ሀገራት አንዷ እንደሆነች ተገለፀ፡፡

ፍሪደም ኦን ዘ ኢንተርኔት 2014›› የተባለው ሪፖርት ባወጣው ደረጃ መሰረት በ 65 ሀገራት ጥናት በማካሄድ የኢንተርኔት መብት የማይከበርባቸውን የመጀመሪያዎቹን አስር ሀገራት አስቀምጧል፡፡
ከእነዚህ ሀገራት ኢትዮጵያ በአምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች እንደ ሪፖርቱ፡፡
የኢንተርኔት ነፃነት የማይከበርባቸው ሀገራት ተብለው ከተቀመቱት እንደ ኢራን፣ ሶርያ፣ ቻይና፣ ኡዝቤኪስታን፣ ቬትናም፣ ባህሬን፣ ሳውዲ አረቢያና ፓኪስታን ያሉ የእስያ ሀገራት ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡
ከአስሩ ሀገራት ኢትዮጵያና ኩባ ብቻ ናቸው የእሲያ ያልሆኑ የኢንተርኔት መብት የሌላቸው ሀገራት፡፡
ዘገባው IBN Live ነው==>
Pakistan is among the 10 worst countries along with Iran and China on the index of internet freedom, according to a global survey released today.
Freedom House released its 'Freedom on the Internet 2014' report, which surveyed 65 countries and listed the index on obstacles to internet access, limits placed on internet content, and violations of internet user rights.
It showed Pakistan at 10th position, one step down from the 11th worst in 2013, an increase in the restrictions imposed on the internet.

ts gradual fall during the past four years continues when it was 13th from the bottom in 2011.
Majority among the top ten worst countries are from Asia, including Iran, Syria, China, Uzbekistan, Vietnam, Bahrain, Saudi Arabia and Pakistan.
Only Cuba and Ethiopia are two others non-Asian among the top ten, placed at fourth and fifth positions.

Tuesday, November 18, 2014



ከጥቂት ጊዜያት በፊት BecauseIamOromo በሚል ርእስ አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተቋም አምነስቲ ኢንተርናሽናል በኦሮሞ ወጣቶች አራማጆች እና ፓለቲከኞች ላይ የሚደርሰውን ሰፊ የመብት ጥሰት በዝርዝር የሚያሳይ ሪፓርት ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ይህ ሪፓርት በተደጋጋሚ የምንሰማቸው የነበሩትን የኦሮሞ ወጣቶች ላይ የሚደርሱ የመብት ጥሰቶቸን በአስደንጋጭ ሁኔታ እና በሚገባ የዘገበ ነው፡፡ ይህ የመብት ጥሰት ዘገባ በተለያዩ አካላት ርእሰ ጉዳይ ተደርጎ ቢነሳም በቂ ውይይት ሊደረግበት ተጨማሪ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል በሚል እሳቤ ከህዳር 4 እስከ 6 ሶስት ቀናት የሚቆይ የበይነ መረብ ዘመቻ አዘጋጅተናል፡፡ ይህ ዘመቻ የሪፓርቱ ርእስ በሆነው ኦሮሞ በመሆኔ (‪#‎BecauseIamOromo‬) በሚል መሪ ቃል ይካሄዳል፡፡
የዚህ በይነ መረብ ዘመቻ ዋና አላማ በኦሮሞ ህዝብ ላይ በመንግስት በሰፊው ያለማቋረጥ እየተካሄደ ያለው የሰብአዊ መብት ረገጣ ለማውገዝ ፣ በመብት ረገጣው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች አጋርነታችንን ለማሳየትና በጨቋኙ ስርአት በኦሮሞ ህዝብ ላይ እየደረሰ ላለው ቀጣይ የመብት ጥሰት ዝም መባል የማይገባው አገራዊ ጉዳይ አንደሆነ ለማሳየት ነው ፡፡ በዚህ ዘመቻ በዘጋቢ ሪፓርቱ ላይ በሰፊው የተጠቀሱ የኢህአዴግ መንግሰት የፈጸማቸውን የመብት ጥሰቶችንም ለማጋለጥ እና ለማሳወቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለን እናምናለን፡፡ በዚህ ዘመቻ ማስተላለፍ የምንፈልገው መልእክት ግልጽ ነው፡፡ የህዝቦች ወንድማማችነት በጨቋኝ ስርአት ውስጥ ጠንክሮ መታየት እንደገባው በአንድ ብሄር ላይ የተነጣጠረ የመብት ጥሰትም የሁሉም ኢትዮጲያውያን ጉዳይ መሆኑን! አንድ አካል ሲነካ መላ ሰውነትን እንደሚያመው ሁሉ ገዢዎቻችን ለይተው የሚያደርሱት ጭቆና የሁላችንም ህመምና ጉዳይ መሆኑን ለማሳየት በዚሀ ዘመቻ ላይ በንቃት እንድትሳተፉ በአክብሮት ተጋብዛችኋል፡፡
ፌስቡክና ትዊተር በዋናነት የዘመቻው ቦታዎች ሲሆኑ፣ የዘመቻው ተሳታፊዎች በሙሉ #BecauseIamOromo መሪ ቃልን አንዲጠቀሙ ከዘጋቢ ሪፓርቱ እና ከሪፓርቱም ውጪ የሚያቋቸውን ታሪኮች አጭር ጽሁፎች(ስታተሶች) እንዲሁም የተሰማቸውን ስሜት በመግለጽ ለዘመቻው የተዘጋጁ ፕሮፋይል ፎቶዎቸን እና የሽፋን ምስሎችን በመጠቀም በዘመቻው ንቁ ተሳታፊ አንዲሆኑ በአክብሮት አንጋብዛለን፡፡ በሶስቱ ቀን የዘመቻ ቆይታ ለዘመቻው ተብሎ የተከፈተው ኤቨንት ገጽ ላይም ሀሳቦችን በመለዋወጥ እና ስለዘመቻው ያላችሁን ሃሳብ አንድትገልጹ በአክብሮት ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡
አንወያይ ሃሳብና ስሜታችንን እናካፍል ጉዳያችን መሆኑን አጋርነታችንን እናሳይ!
 #ኦሮሞ_በመሆኔ #OromooTauukoof #BecauseIamOromo

Friday, October 31, 2014

የአፍሪካ ጸደይ"ኮምፓዎሬ “ደህና ሁኑ”!!!!!



ቡርኪናፋሶን ያለገደብ ሲመሩ የነበሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ ለተጨማሪ ዓመታት ሥልጣናቸውን ለማራዘም ያደረጉት ሙከራ በመክሸፉ ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ ገለጹ፤ ለአንድ ዓመት የመሸጋገሪያ መንግሥት ተመስርቶ ምርጫ እስከሚደረግ በሥልጣን እንደሚቀጥሉ አስታወቁ፡፡ ሕዝቡና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ግን ይህንን የሚቀበሉበት ትከሻ እንደሌላቸውና የኮምፓዎሬ አገዛዝ አሁኑኑ መውረድ እንዳለበት በተቃውሟቸው እየገለጹ ነው፡፡ ከ27ዓመት አምባገነናዊ ሥርዓት በኋላ ቡርኪናፋሶ ወደ ሌላ አምባገነናዊ ሥርዓት ልትሄድ እንደምትች ተጠቆመ፡፡

በቀድሞው ፕሬዚዳንት ቶማስ ሳንካራ ዘመን የመንግሥት ባለሥልጣንና የሳንካራ ወዳጅ የነበሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ፤ ቶማስ ሳንካራ ባልታወቀ ሁኔታ በመፈንቅለ መንግሥት ከተገደሉ ከዛሬ 27ዓመት ጀምሮ ቡርኪናፋሶን መግዛት ጀመሩ፡፡ መፈንቅለ መንግሥቱን በመምራት የተሳተፉት ኮምፓዎሬ የሳንካራን መገደል በወቅቱ “ድንገተኛ” በማለት ከመጥቀስ በስተቀር ምርመራ እንዲካሄድ አላዘዙም፤ ምስጢሩም እንዳይወጣ ተደርጎ ቆይቷል፡፡

ቶማስ ሳንካራን ከሥልጣን ካስወገዱ በኋላ ለሦስት ዓስርተ ዓመታት ያህል የዘለቀውን አገዛዛቸውን የጀመሩት ኮምፓዎሬ እኤአ በ1990ዎቹ በተደጋጋሚ የተመረጡት ሲሆን የአገሪቱ ሕገመንግሥት ከተሻሻለ በኋላ በሁለት ሺዎቹም ሁለት ጊዜ ተመርጠዋል፡፡

በአገዛዝ በቆዩበት ዘመን ሁሉ የአውሮጳውያንና የአሜሪካ ወዳጅ በመሆን ሥልጣናቸው ሳይደፈር በአምባገነንነት ለመቆየት ችለዋል፡፡ አክራሪ እስላማዊነትን እዋጋለሁ በማለት የአሜሪካ ወዳጅነታቸውን ያጠናከሩት ኮምፓዎሬ በላይቤሪያና ሴራሊዮን እጅግ አስከፊ ጭፍጨፋ ያካሄዱትን እና በአሁኑ ወቅት 50ዓመት እስራት የተበየነባቸው የቀድሞው የላይቤሪያ መሪ ቻርልስ ቴለር የቅርብ ወዳጅ ነበሩ፡፡ ሳንካራን ለመገልበጥና ለመግደል የቴይለር ጦር እንደተሳተፈና በምላሹ ኮምፓዎሬ ለቴይለር ወደ ሥልጣን መምጣትና ከዚያ ጋር ተያይዞ ለተፈጸመው ወንጀል ተባባሪ ናቸው በማለት ሁኔታዎችን የሚያገናኙ ወገኖች አሉ፡፡

በአገራቸው የሚነሱ ተቃውሞዎችን ስልታዊ በሆነ መንገድና በምዕራባውያን ድጋፍ ሲያከሽፉ የኖሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ በአካባቢው አገራት ዘንድ የሰላም ዘንባባ አቅራቢ፣ አስታራቂ፣ አስማሚ፣ ሸምጋይ፣ … ሆነው ምስላቸውን እና ማንነታቸውን ሲገነቡ ቆይተዋል፡፡ በአምባገነንነት በቆዩባቸው ዓመታት በሙስና በተለይም ከአልማዝ ሽያጭ ከሚገኘው ገንዘብ ያላቸው ተሳታፊነት ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል፡፡

በቀጣዩ የአውሮጳውያን ዓመት 2015 ሥልጣናቸው የሚያበቃው ኮምፓዎሬ “ደህና ሁኑ” ብለው ለመሄድ የተዘጋጁ አልነበሩም፡፡ በመሆኑም የአገሪቱን ሕገመንግሥት በማሻሻል እንደገና ለመመረጥ ደፋ ቀና ማለት ጀመሩ፡፤ ፓርላማቸውን አሰብስበው ሕገመንግሥቱ እንዲሻሻል በማድረግ ሂደት ላይ እያሉ ሕዝቡ “በቃኝ” አለ፡፡

የ27 ዓመታት አገዛዝ የመረራቸው ዜጎች ሐሙስ ዕለት ፓርላማውን ጥሰው በመግባት ድምጽ እንዳይሰጥ ከማድረግ አልፈው በእሣት አጋዩት፡፡ ተቃውሞ በየቦታው ፈነዳ፡፡ ቡርኪናፋሶ መጋየት ጀመረች፡፡ ሁኔታው ያላማራቸው ኮምፓዎሬ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጁ፡፤ ሰሚ ግን አላገኙም፡፡ ሕዝቡ “ይህንን አገዛዝ አንፈልግም፣ በቃን” አለ፡፡ ሕዝባዊ ዓመጽ በየቦታው ተቀጣጠለ፡፡ በተለይ ዋና ከተማዋ ዖጋዱጉ የዓመጹ ዋና ማዕከል ሆነች፡፡

መንግሥት ሥራ አቆመ፣ ፓርላማውም ፈረሰ፡፡ ድህነት ያስመረራቸው ዜጎች አሁንም ተቃውሟቸውን ቀጥሉ፡፡ ኮምፓዎሬን ማየትም ሆነ መስማት በጭራሽ አይፈልጉም፡፡ ወታደሮች በየአካባቢው ሥነሥርዓት ለማስጠበቅ እየጣሩ ቢሆንም ዓመጹ ግን ቀጥሏል፡፡ ንብረት እየወደመ ነው፤ ባንኮችም ተዘርፈዋል፡፡

ዛሬ አርብ ዳግም ለመመረጥ ሲመኙ የነበሩት ኮምፓዎሬ ሥልጣን በቃኝ፤ መንግሥት ፈርሷል፤ ፓርላማውም አይሰራም፤ ከሥልጣኔ እለቃለሁ ነገር ግን በ2015 ምርጫ እስከሚካሄድ የሽግግር አስተዳደር ተመስርቶ ሁሉም ነገር መረጋጋት አለበት በማለት አስቀድሞ በተቀዳ የቴሌቪዥን መልዕክት ቢያስተላልፉም ሰቆቃ የመረራቸው፣ ኑሮ ያቃጠላቸው፣ ነጻነት የጠማቸው ዜጎች ግን አሁንም “አንሰማም” ብለው ተቃውሟቸውን በመቀጠል ፕሬዚዳንቱ ከሥልጣን እንዲወርዱ ጠይቀዋል፡፡

ሰላሳ አራት የሚሆኑ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ፕሬዚዳንቱ ያቀረቡትን ቅደመ ሁኔታ አንቀበልም ብለዋል፡፡ ለኮምፓዎሬ ምላሽ ሲሰጡም “አንድ የምንቀበለው አጭርና ግልጽ ቅድመ ሁኔታ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ብሌዝ ኮምፓዎሬ ከሥልጣን እንዲለቁ ነው” በማለት ተናግረዋል፡፡

ጦሩ ሥልጣኑን የተረከበ እንደሆነ እየተጠቆመ ሲሆን አገሪቱን በበቂ ሁኔታ ለማረጋጋት እንዳልቻለ ከዋና ከተማዋ የሚመጡ ዜናዎች ይጠቁማሉ፡፡ የሕዝቡ ዓመጽም ወደ ሌሎች ከተሞች እየተዛመተ መሆኑን ከተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች እየተሰማ ነው፡፡

በአንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ዘንድ ከአረብ ጸደይ ቀጥሎ የተጀመረ “የአፍሪካ ጸደይ” ሊሆን ይችላል በማለት ግምት የሰጡበት የቡርኪናፋሶ ሕዝባዊ አመጽ ተመልሶ በአምባገነናዊ አገዛዝ እንዳይወድቅ ስጋት አላቸው፡፡ ለዚህም ጠንካራ ተቋማት መመሥረት አስፈላጊነትን ያሰምሩበታል፡፡ በተለይ ከአምባገነናዊ አገዛዝ ወደ ሕዝባዊ ሥርዓት በሚደረግ ጉዞ በቅድሚያ የሚደረጉ መሰናዶዎች ሳይከናወኑ በጭፍን አምባገነኖችን ከሥልጣን እንዲወርዱ ማድረግ በበርካታ አገራት እንደተደረገው መልኩን የቀየረ አምባገነናዊ ሥርዓት ለመመሥረት እንደሚጋብዝ ይናገራሉ፡፡ ከዚህ አንጻር የሕዝብ ንቃተ ኅሊና መዳበር፣ የእርሰበርስ ውይይት መጀመር፣ የተቋማት መመሥረት፣ … ወሳኝነት ያላቸው ቅድመ ሁኔታዎች እንደሆኑ ያሰምሩበታል፡፡

ይህንን ዘገባ ካጠናቀርን በኋላ ከቢቢሲ የተገኘው ዜና እንደሚያመለክተው ከሆነ ፕሬዚዳንቱ ሥልጣናቸውን ጥለው ከአገር እየወጡ እንደሆነ የጦሩ ጄኔራል ዖኖሬ ትራዖሬ በሕገመንግሥቱ መሰረት አገሪቷን እየመሩ እንደሆኑ አስታውቀዋል፡፡ የፕሬዚዳንቱ ቦታ ባዶ እንደሆነና በ90 ቀናት ውስጥ ምርጫ እንዲካሄድ መነገሩን ቢቢሲ ጨምሮ ዘግቧል፡፡ ብሌዝ ኮምፓዎሬ አሁን ያሉበት ቦታ ባይታወቅም በአቅራቢያ ባለ አገር አቋርጠው ወደ አንድ አውሮፓ ምናልባትም ፈረንሳይ የስደት ህይወታቸውን መምራት ይጀምራሉ የሚል ግምት እንዳለ እየተነገረ ነው፡፡

Wednesday, October 29, 2014

Ethiopian court sentences journalist to three years in prison

Nairobi, October 27, 2014--The Committee to Protect Journalists condemns today's sentencing of Ethiopian journalist Temesghen Desalegn to three years' imprisonment on charges of defamation and incitement that date back to 2012. A court in Addis Ababa, the capital, convicted Temesgen on October 13 in connection with opinion pieces published in the now-defunct Feteh news magazine, according to news reports. He was arrested the same day. Authorities have routinely targeted Temesghen for his writing. Temesghen's lawyer said he plans to appeal the ruling, according to local journalists.


https://cpj.org/2014/10/ethiopian-court-sentences-journalist-to-three-year.php

Saturday, October 11, 2014

እስር ቤት ውስጥ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን መልዕክት!!!

  አቶ በቀለ ገርባን፣ አቶ ኦልባና ሌሊሳን፣ አዛውንቱን ሲሳይ ብርሌን፣ አቶ ጉታ ዋቆንና ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬን አግኝተዋል፡፡ 
‹‹ህብረ ብሄር ፓርቲዎች ተጠናክረው የብሄር ፓርቲዎችን ማጥፋት አለባቸው›› አቶ በቀለ ገርባ
ከዝዋይ ወደ ቃሊቲ ከመጣሁ 11 ወራት ሆኖኛል፡፡ በህዳር ወር 2006 ዓ.ም ነው ወደ ቃሊቲ የመጣሁት፡፡ በአሞክሮዬ መሰረት ጥር 11 ቀን 2006 ዓ.ም መፈታት ቢገባኝም አሁንም ድረስ እስር ቤት ውስጥ እገኛለሁ፡፡ በወቅቱ በአሞክሮዬ መሰረት መፈታት እንዳለብኝ ለእስር ቤቱ ኃላፊዎች ደብዳቤ ጽፌ ነበር፡፡ ሊፉቱ ሲፈልጉ አስጠርተው ያነጋግሩሃል፡፡ ካልፈለጉ ደግሞ ዝም ይሉሃል፡፡ እኔ ደብዳቤ ብጽፍም አልተጠራሁም፡፡ ምክንያታቸውን ባላውቅም ሊፈቱኝ አልፈለጉም ማለት ነው፡፡ ግን በአሞክሮዬ ባለመፈታቴ አልተጎዳሁም፡፡ በርካታ ነገሮችን ተምሬበታለሁ፡፡ እንዲያውም የሚጎዱት እነሱው ራሳቸው ናቸው፡፡ በርካታ ታሳሪዎች አሳሪዎቹ ለቃላቸውም ሆነ በህጉ ተገዥ እንዳልሆኑ በእኔ ጉዳይ ተምረዋል፡፡ አሁን በመጋቢት ወር ዋናውን ፍርድ ጨርሼ እፈታለሁ ብዬ እጠብቃለሁ፡፡
እኔ የማምነው በባለሙያነቴ ነው፡፡ ፖለቲከኛ ነኝ ብዬ አላምንም፡፡ እንደዛም ሆኖ ግን እንደ ግለሰብ ፍትህን እሻለሁ፡፡ ስልጣን ላይ ማንም ይምጣ ማን ፍትህን የሚሰጥ ከሆነ ችግር የለብኝም፡፡ በሙያተኝነቴ ነው መቀጠል የምፈልገው፡፡ ነገር ግን ክፍቶች አሉ፡፡ ወደ ፖለቲካው የገባሁትም ክፍተቶችን በማየቴ ነው፡፡
ህብረ ብሄራዊ የሚባሉ ፓርቲዎች ለአብዛኛው ህዝብ ተደራሽ አይደሉም፡፡ የህብረ ብሄር ፓርቲዎች ድክመት ደግሞ የብሄር ፓርቲዎች እንዲፈጠሩ ምክንያት ሆኗል፡፡ በእነሱ መዳከም ነው የብሄር ፓርቲዎች በየ ቦታው ለመመስረት እድል የሚያገኙት፡፡ ህብረ ብሄር ፓርቲዎች የአንድን ማህበረሰብ ችግር ለመፍታት አቅም የላቸውም ብሎ ያሰበ አካል/ሰው እወክለዋለሁ በሚለው ማህበረሰብ ስም ፓርቲ ያቋቁማል፡፡ እኔም በዚህ ክፍተት ነው ወደ ፖለቲካው የገባሁት፡፡ ይህ ችግር ባይኖር ማህበረሰብን ከፋፍሎ ‹‹ይህኛው ፓርቲ የዚህ፣ ያንኛው ደግሞ የዚህኛው ማህበረሰብ ፓርቲ ነው›› ተብሎ እንዲከፋፈል ፍላጎት የለኝም፡፡
ህብረ ብሄራዊ ፓርቲዎች ቢጠናከሩ በአንድነት መታገልን የመሰለ ነገር የለም፡፡ ከአንዱ ዓለም አራጌ ጋር በታሰርንበት ወቅት ‹‹እናንተ ከተጠናከራችሁ እኛ እንጠፋለን፡፡ እናንተ ተጠናክራችሁ በብሄር የተደራጀነውን ማጥፋት አለባችሁ፡፡ ተጠናከሩና እኛን አጥፉን፡፡ ያኔ ሁላችንም በአንድነት እንታገላለን፡፡ ችግሮችም ይፈታሉ›› እለው ነበር፡፡ የህብረ ብሄራዊ ፓርቲዎች አለመጠናከር እንጅ ለዚህኛው አሊያም ለዛኛው ህዝብ ብዬ መስራት አልፈልግም፡፡ በአንድነት መስራትን የመሰለ ነገር የለም፡፡
ህብረ ብሄር ፓርቲዎች በአንድ በኩል በመረጃ እጥረት፣ በሌላ በኩል በስህተት፣ አሊያም አይቶ በማለፍ የአንድን ማህበረሰብ ችግር ችላ ይሉታል፡፡ ይህ ነው ተነጣጥሎ ለመታገል፣ ለብሄር ፓርቲዎች መበራከት ምክንያት የሆነው፡፡ ህዝብ መብቱ እስከተከበረለት ድረስ ማን መጣ ማን ትኩረት አይሰጥም፡፡ ህብረ ብሄር ፓርቲዎች መዳከም ግን የብሄር ፓርቲዎች ተደማጭነት እንዲያገኙ ምክንያት ሆኗል፡፡ አሜሪካን ለምሳሌ ብንወስድ ህዝቡ መብቱ እስከተከበረለት ድረስ ጥቁር መራ ነጭ ችግር የለበትም፡፡ የእኛ አገርም ጉዳይ ተመሳሳይ መሆን ይችላል፡፡ በዚህ ላይ እኛ ወንድማማቾች ነኝ፡፡
እኔ ህብረ ብሄር ፓርቲዎችን እወቅሳለሁ፡፡ እነሱ ከተጠናከሩ በየቦታው በተናጠል የሚደረገው ትግል ወደ አንድ ጠንካራ ትግል ይመጣል፡፡ እነሱ ከተጠናከሩ በተናጠል የሚደረገው ጭቆና ይቀንሳል፡፡ ክፍተት ባይኖርና ህብረ ብሄር ፓርቲዎች ለሁሉም ህዝብ መድረስ ቢችሉ እኔ በሙያዬ በቀጠልኩ ነበር፡፡ እንዲህ የምንታሰረውም እኩ ከድክመታችን የተነሳ ነው፡፡ ጠንካራ ህብረ ብሄራዊ ፓርቲ ቢኖረን እኮ እኛም አንተሰርም ነበር፡፡ ይህ ካልሆነ ግን የአገራችንን ችግር መፍታት አንችልም፡፡ በተናጠል ለጭቆና እንዳረጋለን፡፡ በተናጠል እንታሰራለን፡፡ በሂደት ጭቆናውን እየለመድነው እንሄዳለን፡፡ በዚህ ሁኔታ ለውጥ ማምጣት አንችልም፡፡
‹‹ኢትዮጵያ ጭንቅ ላይ እንዳለች እርጉዝ ሴት ነች›› አቶ ሲሳይ ብርሌ
የተፈረደብኝ 13 አመት ነው፡፡ ከታሰርኩ አራት አመት ሆኖኗል፡፡ እድሜየ 65 ደርሷል፡፡ እስር ቤት ውስጥ ችግር አለ፡፡ የእስር ቤቱን ኃላፊዎች የምናገኛቸው ህክምና ስንፈልግ ነው፡፡ ነገር ግን የህክምናው ጉዳይ ባይወራ ይሻላል፡፡ በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ በእርግጥ ውጭ ያለው ህዝብም በሰፊው እስር ቤት ውስጥ እንዳለ ነው የሚቆጠረው፡፡ ልዩነቱ የተሻለ ነፋስ ስለምታገኙ፣ ስለምትዘዋወሩና የፈለጋችሁትን ሰውም ስለምታገኙ ነው፡፡
እኛ እያረጀን ነው፡፡ ከእድሜያችን አንጻር በትግሉ ሂደት ብዙም የምንጨምረው ነገር ላይኖር ይችላል፡፡ እናንተ ወጣቶች ናችሁ፡፡ ለትግሉ መሰረት የምትጥሉበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ ወጣትነት ለትግል ወሳኝ ጊዜ ነው፡፡ አባት ያላወረሰውን ልጅ ሊያስቀጥል አይችልም፡፡ እናንተ አሁን ለራሳችሁ ብቻ ሳይሆን ለልጆቻችሁም ጭምር ነው የምትታገሉት፡፡ እናንተ በርትታችሁ ካልታገላችሁ ልጆቻችሁ ምንም የሚወርሱት ነገር አይኖርም፡፡ አባት ያላወረሰውን ደግሞ ልጅ ምንም ነገር ሊያስቀጥል አይችልም፡፡ በመሆኑም እናንተ ከአሁኑ ለእውነት በመቆም ልጆቻችሁ የሚያስቀጥሉት ነገር መስራት አለባችሁ፡፡
ጭቆና እስካለ ድረስ እኔም ሆንኩ እናንተ ባንታገልም ጭቆናውን ለማስወገድ የሚነሳ ሰው አይጠፋም፡፡ እናንተን እድለኛ የሚያደርጋችሁ ጭቆናውን ለመግታት ፈልጋችሁ፣ በራሳችሁ ተነሳሸነት በመጀመራችሁ ነው፡፡
ጭንቅ ላይ ያለች እርጉዝ ሴት ካላማጠች አትገላገልም፡፡ ለእኔ ኢትዮጵያ ጭንቅ ላይ እንዳለች እርጉዝ ሴት ነች፡፡ ኢትዮጵያ አሁን ከሚደርስባት ስቃይ ለመገላገል ማማጥ አለባት፡፡ ያኔ ትገላገለዋለች፡፡ ለዚህ ደግሞ ትግል ያስፈልጋል፡፡ ወጣቶች መታገል አለባችሁ፡፡ ትግሉ ጥንካሬን ይጠይቃል፡፡ መጠንከር አለባችሁ፡፡
‹‹ተቃዋሚዎች በምርጫው ካላመኑበት ሁላችንም አንገባም ማለት አለባቸው›› አቶ ኦልባና ሌሊሳ
የፖለቲካ ፓርቲዎች ስለ ምርጫው ቀድመው መስራት አለባቸው፡፡ ምርጫ ስለመግባት አለመግባት ከመወሰናቸው በፊት ጠንክረው መስራት ይገባቸዋል፡፡ ውሳኔውን ከመወሰናቸው በፊት ውሳኔውን ተከትሎ ሊመጣ የሚችለውን ነገር ማሰብ አለባቸው፡፡ ይህ ጉዳይ ጥናት ያስፈልገዋል፡፡ ለውሳኔያቸው ደግሞ ተገዥዎች መሆን አለባቸው፡፡ አንዴ ከተወሰነ በኋላ ጠንካራ አቋም መያዝ አለበት፡፡ በህዝቡ አመኔታ ለማግኘት በውሳኔያቸው መጽናት አለባቸው፡፡ መወላወል አይገባም፡፡ ጊዜው እስኪደርስ ጠንክረው መስራት አለባቸው፡፡ በአንድ ወቅት 33 የሚባል ስብስብ ነበር፡፡ አሁንም ተባብሮ መስራት ያስፈልጋል፡፡ ለምርጫው በጋራ መስራት ያስፈልጋል፡፡
ተቃዋሚዎች በምርጫው መሳተፍ ለህዝብ የማይጠቅም መሆኑን ካመኑ እና መግባት የማያስፈልጋቸው ከሆነ በአንድነት ኃይልን አሰባስቦ ከምርጫው መውጣት ይቻላል፡፡ በምርጫው ካላመኑበት ሁላችንም አንገባም ነው ማለት ያለባቸው፡፡ በተናጠል ከምርጫው ራስን ማግለል ጥቅም አይኖረውም፡፡ በእርግጥ ይህ መወሰን ያለበት ጊዜው ሲደርስ ነው፡፡ እስከዛ ግን ጠንክረው መስራት አለባቸው፡፡
መጥታችሁ ስለጠየቃችሁን በጣም እናመሰግናለን፡፡ ውጭ ያለውን የቤት ስራችሁንም ጠንክራችሁ መስራት አለባችሁ፡፡
ነገረ ኢትዮጵያ በቀጣይ ጊዜያትም እስር ቤት ውስጥ የሚገኙትን ሌሎች ኢትዮጵያውያን መልዕክት ለማቅረብ ትጥራለች፡፡

Thursday, September 18, 2014

አዲስ ዓመትን በእስር ቤታችን





አዲስ ዓመትን በእስር ቤታችን ………………………..
ያለ ፍትህ ፤ በተራ በቀል ፤ ባሉባልታ ብዙ ብዙ ……..ምክንያቶች መታሰር ለኦሮሞዎች አዲስ አይደለም …….. አዎ ስለ ኦሮሞ እስረኞች ብዙ ተብልዋል እየተባልም ነው፡፡
ኢትዮጵያ የእስር ቤቷ ቋንቋ ኦሮምኛ ነው እስከመባል ዛሬ የአዲስ አመት ዋዜማም አይደል እና እባካችሁ ዛሬ ልለምናችሁ
መቼም ኦሮሞ እንኳን ተለምኖ ሳይለመንም ደግና ቸር ህዝብ ነው ዛሬ በግፍ ለታሰሩብን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ቤተሰቦች እንዲሁም ከመላው የትምህርት ተቋማት ታፍሰው ለታሰሩ ተማሪዎች እና ሙስሊሞች …………
ባገኛችሁት አጋጣሚ እጆቻችሁን ዘርጉላቸው ልጆች ያለ አባት ፤ ሚስት ያለ ባልዋ አዲስ ዓመትን መቀበል እንዴት እንደሚከብድ
ለማስረዳት ይከብዳል ነገ የአቶ በቀለ ባለቤት ትራንስፖር በሌለባት ሀገር ብትችል ከልጆችዋ ጋር አለዝያም ብቻዋን ባለቤትዋን ለመጠየቅ ወደ እስር ቤት
ጉዞ ታደርጋለች ይሄንንም የሚረዳት ካገኘች እንጂ እሷ በምን አቅሟ ………. ህዝቧን ከምታገለግልበት የመምህርነት ሞያዋ ካሰናበትዋት
ቆየች …………………….አዎ
ግፍ ይብቃ ……………. የመረዳዳት ባህላችን ሁሌም ከኛ ጋር ይኑር
መልካም አዲስ ዓመት

Monday, August 25, 2014

መለስን ቅበሩት!



መለስን ቅበሩት!

ከኢትዮጵያ ሀገሬ የደቀቀ ኢኮኖሚ ላይ በማን አህሎኝነት ወጪ ተደርጎ፣ ቅጥ ባጣ መልኩ በመላ አገሪቱ እየተከበረ ስላለው የቀድሞ አምባገነን ጠ/ሚኒስትር ሁለተኛ ሙት ዓመት ዝክርም ሆነ ሰውየውን ዛሬም በአፀደ-ህይወት ያለ ለማስመሰል እየሞከሩ ላሉት ጓዶቹ አንዲት ምክር ብጤ ጣል ማድረጉ ተገቢ ነው ብዬ ስለማስብ በአዲስ መስመር እንዲህ እላለሁ፡-

አብዮታዊው ገዥ-ግንባር ግንቦት ሃያ፣ የህወሓት ምስረታ፣ የብአዴን አፈጣጠር፣ የኦህዴድና የደኢህዴን ውልደት፣ የብሔር ብሔረሰቦች በዓል፣ የባንዲራ ቀን፣ የመከላከያ ሳምንት፣ የፍትሕ ሳምንት፣ የሕዳሴ ግድብ መሰረት ድንጋይ የተጣለበት… ጅኒ-ቁልቋል እያለ ዓመቱን ሙሉ በማይጨበጥ ተራ ፕሮፓጋንዳ ማሰልቸትን መንግስታዊ ኃላፊነት አድርጎታል፡፡ ይህ እንግዲህ ለቁጥር የሚያታክቱ፣ በነጭ ውሸት የታጨቁ እና በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ቅኝት የተንሸዋረሩ ‹ዶክመንተሪ ፊልሞቹ›ን ረስተንለት ነው፡፡


ይህ ሁሉ ያልበቃው ‹‹ጀግናው›› ኢህአዴግ ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ህልፈት ወዲህ፣ ወርሃ-ነሐሴንም እንደ ግንቦት ሃያው ሁሉ የሟቹን ታጋይነትና አብዮታዊነት፤ ሕዝባዊነትና አርቆ አስተዋይነት፤ የርዕዮተ-ዓለም ተራቃቂነትና የአየር ንብረት ተካራካሪነት፤ በፖለቲካ ቢሉ በኢኮኖሚ ቁጥር አንድ ጠቢብነትና ባለራዕይነት፤ ፍፁም ፃድቅነትና ሰማዕትነት…. የሚተረክበት ሲያደርገው ቅንጣት ታህል ሀፍረት አልተሰማውም፡፡ ሰሞኑን በ‹‹ኢትዮጵያ›› ቴሌቪዥን ግድ ሆኖብን ተመልክተንና ሰምተን በትዝብት ካሳለፍናቸው
‹‹መለስ፣ መለስ›› ከሚሉ የከንቱ ውዳሴ አደንቋሪ ድምፆች በተጨማሪ፣ የኦሮሞን ባሕላዊ ልብስ ሲያለብሱት፣ ሐረሪዎች ጋቢ
ሲደርቡለት፤ በደቡብ የሚገኙ ብሔሮች የየራሳቸውን ባሕል የሚወክሉ አልባሳት ሲሸልሙት፣ ስለወላይታነቱ ሲመሰክሩለት… ደጋግመን ለመመልከት ተገደናል፤ ይሁንና ድርጅቱ ስለ ቀድሞ ሊቀ-መንበሩ አልፋና ኦሜጋነት ለመስበክ ዙሪያ ጥምዝ ከዳከረለት ከእንዲህ አይነቱ የተንዛዛ ፕሮፓጋንዳ ይልቅ፣ በዚሁ የቴሌቪዥን መስኮት የቀረበ አንድ ጎልማሳ ‹‹መለስ ሁሉም ማለት ነው›› ሲል የሰጠው አስተያየት፣ ቅልብጭ አድርጎ ይገልፅለት ነበር ብዬ አምናለሁ፡፡ የዚህ አይነቱ ምጥን አስተያየትም በጥራዝ ነጠቅነት ዘላብዶ የኋላ ኋላ በሀፍረት ከማቀርቀር ያድናል፡፡ ለምሳሌ እናንተ የግንባሩ ካድሬዎች ስለመለስ ምሁርነት ለመናገር ስትዳዱ ሁሌ የምትደጋግሙት፣ ያንኑ
የአብዮታዊ ዴሞክራሲ አርቃቂነቱ እና የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ኀልዮት አዋቃሪነቱ ነው፡፡ ግና፣ ይህ ‹‹ንድፈ-ሃሳብ›› ተብዬ ራሱ በርዕዮተ-ዓለምነት ለመጠራት የማይበቃ የተውሸለሸለ ጭብጥ ስለመሆኑ በርካታ ምሁራን በጥናቶቻቸው ከማስረገጣቸው ባሻገር፣ አገሪቷን ለከባድ ኢኮኖሚያዊ ድቀት፣ ሕዝቧን ደግሞ ለጥልቅ ድህነት መዳረጉን ብቻ ማስታወሱ በቂ ይሆናል፡፡ ስለልማታዊ መንግስት አዋጭነት በብቸኝነት እንደተከራከረ ተደርጎ የሚለፈፈውን እንኳን ንቆ መተው ሳይሻል አይቀርም፡፡ ከታንዲካ ማካንደዋሬና መሰል የፅንሰ-ሃሳቡ አበጂዎች የዘረፋቸውን መከራከሪያዎች ማን ዘርዝሮ ይዘልቀውና፡፡ ‹መለስን ቅበሩት› የምለውም፣ እንዲህ ያሉ አስነዋሪ ማንነቶቹን ማስታወስ ስለሚያም ነው፡፡

እናም እውነት እውነት እላችኋለሁ፡- ስለሰውዬው የምትነግሩን እና የምታስቀጥሉት ‹ሌጋሲ›ም ሆነ የምትተገብሩት ረብ ያለው አንድም ራዕይ የለምና ዝም፣ ፀጥ ብላችሁ የምራችሁን ቅበሩት፡፡ እስቲ! ኦጋዴንን ተመልከቱ፤ ካሻችሁም ወደ አኝዋኮች ተሻገሩ፤ ያን
ጊዜ እናንተ በአርያም የሰቀላችሁት ሰው፣ ለነዚህ ሁለት ብሔሮች የቀትር ደም የጠማው ጨካኝ መሪ እንደነበር፣ በክፋት ትዕዛዞቹ ጥፋት ከተረፈ ጠባሳ ትረዱታላችሁ፡፡ ለአቅመ-ሔዋን ያልደረሱ ህፃናት በሰልፍ የሚደፈሩባት፣ ወጣቶች እንጀራ ፍለጋ በተስፋ-ቢስነት ጥልቁን ውቅያኖስ ሰንጥቀው ለመሰደድ የማያመነቱባት፣ የጤና ኬላ ማግኘት ተስኗቸው በልምሻ የሚባትቱ ብላቴኖችን በአቅም-የለሽነትና በቁጭት የምናስተውልባት ደካማ አገር አስረክቦን እንዳለፈ ከወዴት ተሰወረባችሁ? ከቀዬዎቻቸው በጉልበት ለተፈናቀሉ ወገኖች በመቆርቆር ‹‹ሕግ ይከበር!›› ባሉ በየጉራንጉሩ ወድቀው እንዲቀሩ የተፈረደባቸው ጎበዛዝትን ሬሳ እንድንቆጠር ያደረገን ደመ-ቀዝቃዛ
‹መሪ› እንደነበረስ ስንት ጊዜ እያስታወስን እንቆዝም? ቀደምት አባቶች ወራሪውን ፋሽስት ለማንበርከክ የተዋደቁባቸው ጢሻና ኮረብቶች በዚህ ዘመን የዜጎች ወደሞት አገራት መሸጋገሪያ ጽልማሞቶች የሆኑት በማን ሆነና ነው? ከሕግ ተጠያቂነት ቢያመልጥ፣ ከታሪክ ተወቃሽነት ልትታደጉት የምትችሉ ይመስላችኋልን?

…ይልቅ እመኑኝ! ፀጥ ብላችሁ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ጥልቅ ጉድጓድ ቆፍራችሁ ቅበሩት! ላይመለስ በመሄዱም እንደ ግልግል ቆጥራችሁት እርሱት!! መቼም በገዛ ራሱ ሕዝብ ላይ ትውልዶች ይቅር ሊሉት የሚሳናቸውን ይህን መሰሉ መከራ ላዘነበ ሰው በአፀደ- ስጋ ሳለም ሆነ በበድን የሙት መንፈሱ ስር በየዓመቱ ለአምላኪነት መንበርከክ፣ የናንተን አልቦ ማንነት እንጂ ሌላ አንዳች የሚነገረን ቁም ነገር ጠብ ሊለው አይችልም፡፡ ይህም ሆኖ ለመለስ አምልኮ እጅ መስጠት አሳፋሪነቱ፣ ለካዳሚዎቹ ብቻ መሆኑን መስክሮ ማለፉ የቀሪዎቻችን ዕዳ እንደሆነ መገንዘብ አለብን፡፡


ተመስገን ደሳለኝ

Friday, August 22, 2014

ዶ/ር መረራ ጉዲና ከቪኦኤ ጋር ያደረጉትን ቃለ-ምልልስ

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ መሪ ዶ/ር መረራ ጉዲና ባለፈው ሣምንት መጨረሻ ዋሺንግተን ዲሲ ውስጥ በሚገኘው ናሽናል ኢንዶውመንት ፎር ዴሞክራሲ በሚባለው ተቋም ውስጥ ለተሰበሰቡ ታዳሚዎች ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡
የዶ/ር መረራ ወረቀት ርዕስ፡- የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር አንድ እርምጃ ወደፊት፤ ሁለት እርምጃ ወደኋላ” የሚል ነው፡፡
ዶ/ር መረራ በዚህ ፅሁፋቸው ውስጥ ያለፉት 23 የኢሕአዴግ ዓመታት በሦስት ዋና ዋና መንገዶች ፡…ያልተሣኩ ነበሩ…” ብለዋል፡፡
በ23ቱ ዓመታት መጀመሪያ ላይ የተነሡት ሥሉስ ቃላት - “ጎሣን መሠረት ያደረገ ፌደራላዊ ሥርዓት፤ ብዝኀ ፓርቲ ዴሞክራሲና የነፃ ገበያ ምጣኔ ኃብት - አልተከበሩም፤ የከሸፉ ቃላት ሆነዋል” ብለዋል፡፡
መጭውን ምርጫ አስመልክቶ ዶ/ር መረራ ሲናገሩ ተቃዋሚዎች በቀረው ጊዜ ተቃዋሚዎች እንዲተባበሩና ጥንካሬን እንዲፈጥሩ መክረዋል፡፡
ዶ/ር መረራ ጉዲና ከቪኦኤ ጋር ያደረጉትን ቃለ-ምልልስ ሙሉ ቃል ያዳምጡhttp://amharic.voanews.com/content/ethiopia-politics-interview-with-dr-merera-gudina-of-medrek-07-19-14/1961194.html

Thursday, July 17, 2014

ሰበር ዜና:- ጦማሪያኑና ጋዜጠኞቹ ላይ ክስ ተመሠረተ



ሰበር ዜና:- ጦማሪያኑና ጋዜጠኞቹ ላይ ክስ ተመሠረተ

በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ውለው የነበሩት ጦማሪያን፣ ሶልያና ሽመልስ (በሌለችበት)፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ አጥናፉ

ብርሃኔ፣ ዘለዓለም ክብረት፣ አቤል ዋበላ፣ እንዲሁም ጋዜጠኞቹ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሣዬና ተስፋለም ወልደየስ ላይ ሐምሌ 10 ቀን 2006 ዓ.ም. ክስ ተመሠረተ፡፡





እኔን ያልገባኝ ተሸባሪው ማነው?ያወራ አሸባሪ የፃፈ አሸባሪ ተቃወሚወች አሸባሪ ህዝቡ ሀሉ አሸባሪ ከሆነ ማነው ተሸባሪ?
 
 
 

Saturday, July 5, 2014

የዓለም ባንክ በተያዘው አመት በታሪኩ ከፍተኛ የገንዘብ መጠን ለኢትዮጵያ ማስተላለፉ ተገለጸ!

 


የዓለም ባንክ በተያዘው አመት በታሪኩ ከፍተኛ የገንዘብ መጠን ለኢትዮጵያ ማስተላለፉ ተገለጸ

መቀመጫውን በዋሽንግተን ያደረገው የዓለም ባንክ በተያዘው ዓመት ባንኩ በታሪኩ ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ድጋፍ እና እርዳታ ማድረጉን የሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ አመልክቷል፡፡

ጋዜጣው በተያዘው ዓመት ብቻ የዓለም ባንክ 1.6 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ለኢትዮጵያ ማስተላለፉን ጠቅሷል፡፡
እኔ የምለው ከዓለም በድህነት 2ኛ?የሄ ሁሉ ገነዘብ የትገባ'?

Tuesday, July 1, 2014

BREAKING NEWS]OLF merged under leadership of Dawud Ibsa with Dhugassa Bakako as deputy!

OLF declares a merge between OLF-QC and OLF-SG

June 28, 2014 (Oromo Liberation Front) — It is with great pleasure that we announce to our people and the supporters of our struggle for freedom the good news that, based on the accord they made in Kampala, Uganda, in November 2012, the two organizations of the Oromo Liberation Front (OLF) known as OLF Shanee Gumii (”OLF National Council”) and OLF Qaama Ce’umsaa (”OLF Transitional Authority”) have resolved our differences and agreed to combine our two leaderships, unify our members, merge our organizational structures and inaugurate a reunified OLF. Although OLF has encountered many obstacles during the last forty years, there was no time when it has stopped the struggle that it was established to lead. No one can deny the fact that the national struggle led by the OLF has scored many victories and made many significant achievements that have taken the Oromo people a long way toward the national goal of independence. Among these great achievements is the level of political awareness of our people.
At the same time, we witness that the Oromo people are being targeted for extinction more than any time before. Oppression has reached intolerable levels making our people to rise up in defiance of tyranny, protesting peacefully in all corners of Oromia. But, as witnessed in the killings of students and others in many places in Oromia, the TPLF regime is responding violently to their lawful demands. Defying enemy atrocities, imprisonment, and torture the young Oromo generation are making it known to the world that they will not tolerate humiliation and oppression anymore and that they will make the necessary sacrifices to liberate their people and homeland from alien oppressors. The OLF extends its condolences to families who lost their beloved sons daughters and expresses its admiration for the courage and bravery they have shown by the young Oromo generation to defend their people’s legitimate rights. As the vanguard of the Oromo struggle for freedom, we re-iterate our determination to continue the struggle until our people become masters of their destiny.
The re-unification of the two organizations of the OLF is a great step that will strengthen the Oromo struggle for freedom. United under one leadership, we are resolute to realize the principal objective of our struggle, namely the liberation of our people and the independence of our homeland Oromia. There is no question about the popularity of the goal of OLF-led liberation struggle among the Oromo people. Therefore, it is with determination that we pledge to make the necessary sacrifices, withstand the challenges ahead and carry through the Oromo national struggle to the ultimate goal of independence.
We are well aware that there are Oromo nationals who are organized separately under other names to advance our people’s legitimate rights. We will do all we can to coordinate our efforts with them to achieve the common goal. The OLF leadership states its decision and commitment to continue to work and conclude the ongoing talks with other forces committed to the same goal. Hence we call on all Oromo organizations that uphold our people’s right to self-determination and independence to join us in carrying out this sacred mission.
We also take this opportunity to express our solidarity with the oppressed nations, nationalities and peoples who are struggling for justice against the same tyrannical regime, and call upon them to join us in the common struggle for basic human and democratic rights.
The TPLF-led regime’s violence against the Oromo people is abetted by military, political and economic assistance from external powers. The OLF appeals again to governments, both in the West and East to strike a balance between their national interests and their international obligation of protecting human rights and stop giving economic, military and political support to a brutal regime that is evicting our people and others from their land and killing innocent civilian who are peacefully demanding their legitimate rights.
Victory to the Oromo People!
Oromo Liberation Front
June 28, 2014

Monday, June 9, 2014

ነቀምቴ ላይ አራት ከፍተኛ ሐኪሞች ታሥረዋል?

ዶ/ር አዳም ለማ፤ የቀዶ ሕክምና ሐኪም፣ ዶ/ር ኢሣያስ ብርሃኑና ዶ/ር በላይ ቤተማርያም የማኅፀንና የፅንስ ስፔሻሊስቶች፣ ዶ/ር ታመነ አበራ፤ ቀድሞ የሆስፒታሉ የሕክምና ዳይሬክተርና አሁን ለስፔሻላይዜሽን የጥቁር አንበሣ ሬዚደንት ሐኪም፣ እንዲሁም ዶ/ር ሪም ጆንግ ሆ፤ ኮርያዊ የአጥንት ሐኪም፡፡
ሁሉም በነቀምቴ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ አገልግለዋል፡፡

ዛሬ ኮርያዊው ሐኪም ከሥራ ሲሠናበቱ አራቱ ኢትዮጵያዊያን ግን በቁጥጥር ሥር ውለው ነቀምቴ በሚገኘው ማረሚያ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፡፡

የእነዚህ ለረዥም ዓመታት አገልግሎት ሰጥተዋል የሚባሉ ሐኪሞች ከሥራቸውና ከደመወዛቸው መታገድ፣ አልፎም መታሠር መነጋገሪያ እየሆነ ነው፡፡

“ጥፋታቸው” የተባለው ምን ይሆን? በአካባቢያቸው ያሉ ሰዎችስ “ጥፋተኛ ናቸው” ብለው ያምናሉ?

የተያያዘው ዘገባ የፖሊስን፣ የሆስፒታሉን አስተዳደር፣ የእሥረኞቹን ሐኪሞች ቤተሰቦችና ጠበቃ የሚሉትን ይዞ ዝርዝር መረጃ ይሰጥዎታል፡፡
ያዳምጡት፡

ቪኦኤ

http://amharic.voanews.com/content/nekempte-doctors-arrested/1635248.html 

ጥፋተኛ ናቸው” ብለው ያምናሉ? ????

 

Wednesday, May 28, 2014

ከግንቦት ሃያ ፍሬዎች?



There are tentative signs that the people of Ethiopia are beginning to organize themselves and stand up against the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) government, a brutal dictatorship, albeit one dressed in Western democratic garb.

After 23 years of suppression at the hands of the EPRDF, simmering discontent and anger appear to finally be spilling over onto the streets. Robbed of hope, the people have had enough, enough of the wide-ranging human rights abuses, the denial of constitutional rights, the arbitrary imprisonments and torture, the regime violence, the displacement of people from ancestral land, the partisan distribution of aid and the rising cost of living.

The government’s heavy-handed reaction to the Oromo protests is but the latest example of the regime’s ruthless response to criticism of its policies. Political opposition parties, when tolerated at all, have been totally marginalized, dissenting independent voices are quickly silenced and a general atmosphere of fear is all pervading. Despite freedom of expression being a constitutional right, virtually all media outlets are either government owned or controlled; “blogs and internet pages critical of the Ethiopian government are regularly blocked and independent radio stations, particularly those broadcasting in Amharic and Afan Oromo, are routinely jammed,”Human Rights Watch says.

The EPRDF has created “one of the most repressive media environments in the world”. Reinforcing this condition, “the government on 25 and 26 April arbitrarily arrested nine bloggers and journalists in Addis Ababa. They remain in detention without charge,” Human Rights Watch reports.

International human rights groups (whose activities have been severely restricted by the stifling Charities and Societies Proclamation of 2009) as well as foreign journalists are not welcome, and reporters who attempt to reach demonstrations are turned away or detained, making it difficult to confirm the exact numbers of those killed by government security personnel.

The UN Human Rights Council recently reviewed Ethiopia’s human rights record under the Universal Periodic Review.

Since the first review in 2009 the human rights situation has greatly deteriorated. The EPRDF rules the country through fear and intimidation, it has introduced ambiguous, universally condemned legislation to control and intimidate – the Charities and Societies Proclamation law and the Anti-Terrorism Proclamation especially.

Freedom of assembly – another constitutional right – is not allowed or, as can be seen with the Oromo protests, is dealt with in the harshest manner possible.

The Internet and telecommunications are controlled and monitored by the government and phone records and recordings are easily obtained by security personnel.

Arbitrary arrests and false Imprisonment of anyone criticizing the government is routine as is the use of torture on those incarcerated.

In the Ogaden region the regime is committing gross human rights abuses which constitute crimes against humanity, and in Gambella and the Lower Omo Valley large numbers of indigenous people have been forcibly moved into government camps (villagization programme), as land is sold for pennies to international companies.

In short, human rights are completely ignored by the government in Ethiopia.

As the people begin to come together and protest, international pressure should be applied on the regime to observe the rule of law and uphold the people’s fundamental human rights.

We are living in extraordinary times, times of opportunity and change, times of great hope. With elections due next year, now is the time for the various ethnic groups and factions inside and outside Ethiopia to unite, speak with one voice and demand their rights to freedom and justice.

Sunday, May 18, 2014

ላለፉት 23 ቀናት ክሥ ሳይመሠረትባቸው ታስረው ከሚገኙት ዘጠኝ የዞን ዘጠኝ የኢንተርኔት ሚድያ ፀሐፊዎች የሆኑ ጋዜጠኞችና አምደኞች ስድስቱ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል!

zone9-e1398747809895


ላለፉት 23 ቀናት ክሥ ሳይመሠረትባቸው ታስረው ከሚገኙት ዘጠኝ የዞን ዘጠኝ የኢንተርኔት ሚድያ ፀሐፊዎች የሆኑ ጋዜጠኞችና አምደኞች ስድስቱ ዛሬ፤ ቅዳሜ፣ ግንቦት 9/2006 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበዋል

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ስምንተኛ ወንጀል ችሎት የጋዜጠኞቹንና የአምደኞቹን ጉዳይ ያየው በዝግ ሲሆን የቀረቡት ጋዜጠኞቹ አስማማው ኃይለጊዮርጊስ፣ ተስፋዓለም ወልደየስ እና ኤዶም ካሣዬ እንዲሁም ሌሎች ሦስት አምደኞች መሆናቸው ታውቋል፡፡




የዞን-9 ጋዜጠኞችና ብሎገሮች አራዳ ፍርድ ቤት ቀረቡ




ዛሬ ችሎት ያልቀረቡት አምደኞች መቼ እንደሚቀርቡ ለጊዜው በትክክል ባይታወቅም ሰሞኑን ይቀርባሉ የሚል ጭምጭምታ ተሰምቷል፡፡

የስምንት ታሣሪ ጋዜጠኞቹንና አምደኞቹን ፖሊስ በሽብር አድራጎት እንደሚጠረጥራቸው ለችሎቱ አስታውቆ ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ  የ28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቆባቸዋል፡፡





አራዳ ፍርድ ቤት




ፍርድ ቤቱም የፖሊስን ጥያቄ ተቀብሎ የ28 ቀናቱን የጊዜ ቀጠሮ መስጠቱንና ጉዳዩንም ለፊታችን ሰኔ 7/2006 ዓ.ም መቅጠሩን ተከላካይ ጠበቃው አቶ አምሃ መኮንን ገልፀዋል፡፡

Thursday, May 1, 2014

ETHIOPIA :Dozens of Ethinic oromo students protesters killed!


At least a dozen protesters have been killed and many others wounded as students in Ethiopia's populous Oromia region clashed with military forces on Wednesday.
Student protests began earlier this month in response to plans by Addis Ababa City Administration which is expected to significantly expand the city's territorial jurisdiction.
Thousands of Oromo students at nine universities in Oromia have rallied in the last ten days opposing the plan, which they say would displace Oromo farmers and undermine their state's constitutionally protected "special interests." Oromo students at Jimma, Haromaya, Ambo, Wollega, Bule Hora, Madawalabu, Metu, Adama and Dire Dawa universities have turned out in droves denouncing the plan. At least 20 students were killed in Ambo while three others were shot dead at Madawalabu University on Wednesday, according to eyewitnesses. Unknown number of wounded protesters were being treated at local hospitals. 
The Ethiopian capital falls within the Oromia state, the largest of Ethiopia's nine ethnic-based administrative regions, and also serves as its capital. The country's constitution stipulates the state's special interest in the city — providing for utilization of resources, service provision and joint administration matters. Protesters say the city's latest master plan undermines these interests. 

Sunday, April 27, 2014

Ethiopian Security Forces Open Fire on Students

There has been widespread protest by Oromo students in universities in Ethiopia against unpopular 'Addis Ababa-Finfinnee surrounding integrated master plan'. Oromo students in Haromaya, Jimma, Ambo and Wollega universities held protests.

Although officials in Oromia state and Addis Ababa city administration insist the plan only intends to develop Addis Ababa and its surrounding, Oromo students and the wider Oromo elites believe the plan is to displace farmers in the outskirts and suburban areas of the city, meet the growing demand for land, and weaken the Oromo identity. The Ethiopian constitution grants a special interest to the Oromia state regarding administrative, resource and other socio-economic matters in Addis Ababa, in its article 49 which never have been implemented. This has largely resulted in significant resistance within the ruling party, OPDO, in Oromia and a continues pressure to materialize the implementation.

The protest against the doomed to fail master plan is held in four universities sofar. Yesterday (26/04/2014) at Wollega University, the infamous and notorious Federal police opened fire at innocent Oromo students. Reports and eye witness indicate unknown number of students were hurt and some have fled to the bushes. The people of Nekemete town were prevented from joining the resistance. Even then some of the residents broke through line of federal police force and joined the protest.

At similar protest in Jimma university, the security forces picked more than 10 students and jailed them. Further 15 students in Ambo university were jailed.

The uproar against the plan is resonating across different segments of Oromo society. A singer by name Jafar Yusuf was jailed last week that is believed to be because he released a single condemning the plan. The diaspora is is voicing its concerns through the newly launched diaspora based Oromia Media Network

The security forces in Ethiopia are dominated by the Tigrayan minority who have been in power since the downfall of Derg communist regime in 1991. The Oromos are the most prosecuted in Ethiopia. More than 40000 Oromos are in jail, although the correct figure is hard to know.

Friday, April 25, 2014

The Oromo are Ethiopia’s largest ethnic group, 30 million, and their language is the fourth most spoken in Africa. Yet they are an invisible ethnicity in the eyes of the world

In August 2011, Bekele Gerba, an English teacher at Addis Ababa University and prominent politician, met with a delegation from Amnesty International to discuss the human rights situation in Ethiopia. Gerba, a vocal activist on behalf of his largely Muslim Oromo people, was deputy chairman of the opposition party Oromo Federalist Democratic Movement (OFDM) and a member of the executive committee of Medrek, the country’s main opposition coalition.


To the Ethiopian government, however, Gerba was a terrorist. Four days after the meeting, he was arrested. In November 2012 Gerba was convicted and imprisoned under Ethiopia’s 2009Anti-Terrorism Proclamation for association with the banned Oromo Liberation Front (OLF), which the government has asserted is linked with al-Qaeda affiliated entities. 
According to organisations like Amnesty International and Human Rights Watch, however,Gerba was guilty of being Oromo and talking of the plight of his people. Shortly before hisarrest, Gerba had described the challenges facing his community, telling Voice of America “Anyone who speaks the [Oromo] language and does not belong to the ruling party is a suspect and can be taken to prison any time.” Gerba and other incarcerated Oromo (Oromo rights groups estimate there are around 20,000 Oromo political prisoners in Ethiopia) continue to spark protests in Ethiopia and across the global Oromo diaspora.

Friday, April 11, 2014

ጋዜጠኝነት ለኢትዮጵያ ኢትዮጵያም ለጋዜጠኝነት የማትመች አገር



….ጋዜጠኝነት ለኢትዮጵያ ኢትዮጵያም ለጋዜጠኝነት የማትመች አገር መስላለች፡፡ ብእርን የጨበጡ፣ በሀሳባቸው ብልጫ ውድድሩን ለማሸነፍ የጣሩ፣ ሀሳባቸውን በጽሁፍ ሆነ በንግገር መግለጣቸው እንደነውር ተቆጥሮ ዶክመንተሪ የሚሰራባት፡፡ ሰብዓዊ መብት፣ፍትህ፣እኩልነት እነደማዕድን ተቆፍሮ እንኳን የማይገኝባት ሀገር ሆናለች ኢትዮጵያ፡፡
….ዲሞክራሲ እንደ ሰማይ የራቃት፣ ችጋር ስጋዋን አልፎ አጥንቷን መብላት የጀመረባት፤ ለለውጥ የተነሱ አብረን ተባብረን ወደ ፊት እንራመድ ያሉ እንደ አረም እየተመነጠሩ የሚታሰሩባት ሀገረ መከራ ሆናለች ኢትዮጵያ፡፡
….አንድነቷ ተጎንጉኖ የዘር እራቁትነት የለበሰች፣ ነገ እርስ በእርስ እንዳንበላላ የምታሰጋ፣ ጎጠኝነት እራቁቷን ያስቀራት፣ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ትምክህተኛ ሆኖ የሚፈረጅባት የመከራን ቁልቁል የምትጋልብ ሀገር ሆናለች ኢትዮጵያ፡፡
….ብሄራዊ መግባባት የጠፋባት፣ ሌላውን ላለማስገባት ሁሉም በሩን የዘጋበት፣ የሀገር ትርጉም የጠፋባት፤ ስለ ሀገር ሲጠየቅ ‹‹ምን አገባኝ›› የሚልን ተረት ተናጋሪ የበዛባት ሀገር ሆናለች ኢትዮጵያ፡፡
….ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከራሳቸው ጋር መታረቅ አቅቶቸው አብሮቸው እየሮጠ ያለውን ጠልፈው የሚጥሉባት፣ ተገረፍን ታሰርን እያሉ በሰበብ አስባቡ አገር የሚለቁባት፡፡ ከዚህም የተነሳ ለውጥ ፈላጊው ህዝብ የተቃውሚ ፓርቲዎችን ጭመር በጥርጣሬ የሚያይባት፡፡ ለተቃዋሚም ለመሪም ያልታደለች፣ የመንግስት ለውጥ እንጂ እውነተኛ ለውጥ ያልሰመረላት አገር ኢትዮጵያ፡፡
…..ዛሬም ልጆቿ ይታሰራሉ፣ያለከልካይ ከቦታቸው ይፈናቀላሉ፣ ይደበደባሉ አካላቸው ይጎላል፡፡ሙስና የመጨባበጥ ያህል የቀለለባት፣ከደሀ 10 ካ.ሜ ተነጥቆ ለባለ ገንዘብ 10,000 ካ.ሜ የሚሰጥባት፡፡ ዜግነት በገንዘብ እና በአሸርጋጅነት (በተለጣፊነት) የሚከበርባት ሆናለች ሀገሬ ኢትዮጵያ፡፡
…..የሀይማኖት መሪዎች ‹‹እ/ር የእውነት አምላክ ነው፡፡ ሀሰትም በሱ ዘንድ የለም፡፡›› የሚለውን ሰርዘው በሀይማኖት ካባቸው ስር ሀሰትን ያቀላጥፋሉ፡፡ አደግን፣ ሄድን፣ ደርሰናል እያሉ የምድር ጥቅማቸውን ተምነው ይመላለሳሉ፡፡ አረ እንደውም እ/ር ነጻነታችንን ሰጠን እያሉ በየድንኳኑ የሚጮሁም አሉ፡፡ ማን ነበር ልማታዊ ፓስተር ነኝ ያለው??
‹‹እኛ የሰማይ ቤት አለን የምድሩ የእኛ ስላልሆነ እኛን አይመለከተንም›› የሚሉ ፖለቲካ ለሀጢያን የተተወ ስራ እንደሆነ የሚቆጥሩ ምእመናን እና አስተማሪዎች የተበራከቱባት ሆናለች አገራችን ኢትዮጵያ፡፡
ሙሁሮቿ የት ጠፉ???
ውስጣችን የተፈጠረው ዘረኝነት ከየት መጣ???
ዛሬም ከአለም የታችኛው ተርታ ለምን ተሰለፍን???
የተማረና ያለተማረ ሰው መሀል ያለው የኑሮ ልዩነትስ ምን ያህል ነው???
ኢትዮጵያዊ ሆነን ተፈጥረን፤ የታል ታዲያ ኢትዮጵያ ለኛ የሆነችው??? ችግር፣ረሀብ፣ፍርሀት… ከተፈጠሩባት ሀገራቸው አሰድዶአቸው በሀገር ናፍቆት ሌላ አገር ላይ የሚኖሩ ስንቶች ናቸው??
እውነት እውነቱን ብናወራ በዚህ አካሄዳችን የአትዮጵያ የወደፊት ተስፋ ብሩህ ነውን???
እነዚህ ጥያቄዎች እንደ ማለዳ አንቂ አላርሞች ዙሪያችን ላይ በእየለቱ ይጮሀሉ፤፤
ጉዳዩ አሁን እንደ ጣውንት የቆመውን ስርአት መቀየር ብቻ አይደለም፡፡ የራሳችንንም የአስተሳሰብና የአመለካከት ደጅ መቀየር ያለብን ይመስለኛል፡፡
By Robel Ayalew

Monday, March 31, 2014

የኢትዮጵያ መንግስት በዜጎቹ ላይ ስለላ ያካሄዳል ሲል አንድ የሰብአዊ መብት ቡድን ገለጸ

Thursday, March 20, 2014


US slams Ethiopia’s human rights abuse

(OPride) — The United States in a scathing report on Thursday accused Ethiopia of curtailing freedom of expression and association, using politically motivated trials, harassment and intimidation of activists and journalists.

Ethiopia holds estimated 70,000-80,000 persons, including some 2,500 women and nearly 600 children incarcerated with their mothers, in severely overcrowded six federal and 120 regional prisons, the U.S. said in its voluminous 2013 Human Rights Reportreleased by Secretary of State John Kerry. “There also were many unofficial detention centers throughout the country, including in Dedessa, Bir Sheleko, Tolay, Hormat, Blate, Tatek, Jijiga, Holeta, and Senkele,” the report said.

While it said pretrial detention in local police stations were marred with poor hygiene and police abuse, the report also highlighted impunity for security forces who often commit politically-motivated killings against dissidents and opposition party members as “a serious problem.” The Ethiopian government rarely, if ever, took actions “to prosecute or otherwise punish officials who committed abuses other than corruption,” the report added.

The report named some of the well-known political prisoners and journalists including Eskinder Nega, Bekele Gerba, Olbana Lelisa, Reeyot Alemu and Woubeshet Taye.“Federal Supreme Court upheld the 2012 convictions under the criminal code of Bekele Gerba and Olbana Lelisa, two well-known political opposition figures from the Oromo ethnic group, for conspiracy to overthrow the government and conspiracy to incite unrest,” the report noted.



“The Supreme Court subsequently determined the Federal High Court did not consider mitigating circumstances and reduced Bekele’s sentence from eight years to three years and seven months. The Supreme Court also reduced Olbana’s sentenced from 13 to 11 years. Courts convicted 69 members of Oromo political opposition parties, charged separately in 2011 under the criminal code with “attacking the political or territorial integrity of the state.”

Gerba, who has fully served out his reduced time, was widely expected to be released last month. However, according to family sources, prison officials gave conflicting reasons for his continued imprisonment, including that his time at the Maekelawi prison doesn’t count or his file was misplaced. Meanwhile, both Gerba and Lelisa are reportedly ill with restricted and limited medical care.

Terminally ill

Lelisa is a longtime Oromo rights activist with Oromo Peoples Congress (OPC), who rose through the ranks of the organization from a sole member to top leadership. He competed in the last three elections representing the Caliya district in West Shewa. He was elected to the Oromia regional parliament in 2005. He was subsequently arrested on concocted charges of plotting to overthrow government by working with the Oromo Liberation Front (OLF), recruiting youth for armed rebellion and for inciting the frequent youth revolt in Ambo and West Shewa.

Lelisa, who has so far served three years of the 11 years sentence, reports being mistreated while in prison. He has repeatedly been beaten by unidentified men at Kaliti prison with orders from security services. He has sustained serious wounds from the beatings by government agents who pose as prisoners, according to OPride sources. Lelisa, who is terminally ill and said to be on a long-term medication for undisclosed condition, had repeatedly appealed to the higher court about his mistreatment but received no response to date.

Singling out the Oromo

While the State Department’s report is short on details, there are several evidences that show the Ethiopian government continues to single out Oromo dissidents. Last year, the OLF released a partial list (independently verified by a reputable OPride source) of 528 individuals sentenced to death and life imprisonment on purely political grounds.

The list includes names of individuals, their gender, and ethnic backgrounds. Underscoring the disproportionate repression of the Oromo, of the 528 individuals who were sentenced to death or life imprisonment by the Ethiopian courts, 459 are Oromo nationals followed by 52 Amhara nationals. “This list clearly indicates that the minority regime in Ethiopia is using its kangaroo courts for destroying Oromo and Amhara nationals who are viewed as potential threat to the regimes hold on to power,” one informant, who asked not to be named, told OPride.


As documented by various international human rights organizations, today, it is a serious crime, under the Tigrean dominated Ethiopian government to support any independent Oromo organization. Thousands of Oromos have been imprisoned, tortured and killed extra-judicially for no apparent reason other than expressing Oromo national feeling and for their support of Oromo organizations such as the OLF.

The selective and systematic targeting of Oromo in Ethiopia by the current began in 1992 when the OLF which jointly ruled Ethiopia from 1991-1992 with the Tigrayan Liberation Front (TPLF) was banned and its members and supporters jailed for years and hundreds executed without due process of law. Although Oromia, the Oromo regional state in Ethiopia, is autonomous in name, the Oromo do not have any meaningful voice in the affairs of their own state, which is totally controlled by the TPLF.

The later represents no more than seven percent of the population of Ethiopia, while the Oromo, who constitute the single largest national group in Ethiopia and the third largest national group in the whole of Africa. The Oromo are denied the basic democratic rights to organize freely and legally and express their political opinions. There is no single independent newspaper or media outlet catering to the Oromo populace in their native tongue.

The TPLF fears the Oromo numerical strength deliberately characterizes all independent Oromo organizations, which it does not control as the “terror wing” of the OLF. The goal for such characterization is to persecute peaceful supporters of the OLF behind the façade of fighting against a “ terrorist organization.” Under the anti-terror law of the current Ethiopian regime, anyone who is suspected of peacefully supporting the OLF, could be sentenced to life imprisonment or executed. The above mentioned 459 Oromo nationals who were sentenced to death or life imprisonment are all suspected OLF supporters.



Destroying the lives of 528 innocent human beings on political ground is a crime against humanity, which must be condemned by all civilized nations. The tearless cry of the U.S. AnnuaL Human Rights report notwithstanding, at this moment no calling is more urgent and more noble and no responsibility greater for those who believe in human rights than raising their voice for pressuring the government of Ethiopia to free the 528 innocent individuals who were sentenced to death and life imprisonment on purely political grounds.

In the last year alone, two Oromo activists have died in prison under mysterious circumnances. Last year, OPride reported about the death in prison of former UNHCR recognized refugee, engineer Tesfahun Chemeda. Last month, a former parliamentary candidate from Chalenqo in Western Hararghe, Ahmed Nejash died in prison. According to an OPC source, Nejash successfully run and challenegd Sufian Ahmed, Ethiopia’s Minister of Finance and Development, during the 2010 elections. He was subsequently arrested in 2011 alleged of being an OLF activist. Although his death recieved scant media coverage even within the Oromo community, a close relative of the late Jarra Abba Gadaa, Nejash is one of the veterans of Oromo people’s struggle. “He was sentenced to seven years, which was also upheld by the higher court,” the OPC source told OPride. “He was in Zuway with Bekele and Olbana and he was healthy the last time I saw him in 2013.