Thursday, September 18, 2014

አዲስ ዓመትን በእስር ቤታችን





አዲስ ዓመትን በእስር ቤታችን ………………………..
ያለ ፍትህ ፤ በተራ በቀል ፤ ባሉባልታ ብዙ ብዙ ……..ምክንያቶች መታሰር ለኦሮሞዎች አዲስ አይደለም …….. አዎ ስለ ኦሮሞ እስረኞች ብዙ ተብልዋል እየተባልም ነው፡፡
ኢትዮጵያ የእስር ቤቷ ቋንቋ ኦሮምኛ ነው እስከመባል ዛሬ የአዲስ አመት ዋዜማም አይደል እና እባካችሁ ዛሬ ልለምናችሁ
መቼም ኦሮሞ እንኳን ተለምኖ ሳይለመንም ደግና ቸር ህዝብ ነው ዛሬ በግፍ ለታሰሩብን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ቤተሰቦች እንዲሁም ከመላው የትምህርት ተቋማት ታፍሰው ለታሰሩ ተማሪዎች እና ሙስሊሞች …………
ባገኛችሁት አጋጣሚ እጆቻችሁን ዘርጉላቸው ልጆች ያለ አባት ፤ ሚስት ያለ ባልዋ አዲስ ዓመትን መቀበል እንዴት እንደሚከብድ
ለማስረዳት ይከብዳል ነገ የአቶ በቀለ ባለቤት ትራንስፖር በሌለባት ሀገር ብትችል ከልጆችዋ ጋር አለዝያም ብቻዋን ባለቤትዋን ለመጠየቅ ወደ እስር ቤት
ጉዞ ታደርጋለች ይሄንንም የሚረዳት ካገኘች እንጂ እሷ በምን አቅሟ ………. ህዝቧን ከምታገለግልበት የመምህርነት ሞያዋ ካሰናበትዋት
ቆየች …………………….አዎ
ግፍ ይብቃ ……………. የመረዳዳት ባህላችን ሁሌም ከኛ ጋር ይኑር
መልካም አዲስ ዓመት