Saturday, December 19, 2015

የመንግሥት ኃይሎች ኦሮሚያ ውስጥ እየወሰዱ ያሉት እርምጃ “እጅግ አስከፊ” ወይም በእንግሊዝኛው ቀጥተኛ አባባል “ብሩታል

"ጥቂቶች በብርሀን ፍጥነት ተዝቆ ወደማያልቅ ሀብት የተመነጠቁበት መንኮራኩር፣ መሬት "

ከ5 ዓመታት በፊት እኚህ ክቡር ሰው ሲናገሩ መስሚያ ጆሮ ቢኖራችሁ ዛሬ መያዣ መጨበጫ ባልጠፋችሁ። በነገራችን ላይ ይህ የአቶ በቀለ ገርባ ንግግር እና የአቶ አንዷለም አራጌ ንግግር ምንጊዜም ልቤን የሚያነሳሳኝ፣ በሀገሬ ተስፋ ከሚሰጡኝ መሳጭ ንግግሮች ዋነኞቹ ናቸው

ሀገር መምራት ቀላል እንዳልሆነ እናውቃለን ነገር ግን ከዓመት ዓመት የሕዝቡን ብሶት እያዳመጠ እየተሻለው፣ ልምድ እየቀሰመ ሀገሪቱን ሕዝቡን ወደፊት ማራመድ ሲገባው ከዕለት ወደ ዕለት ወደኋላ እየተመለሰ፣ የኋሊት እየሄደ ሀገሪቱን መምራት ወደማይችልበት ደረጃ ደርሷል::

የኤፌድሪ ሕግ መንግስት እንደሚናገረው ፣ የገዢው ሥርዓት የፖሊሲ ሰነድ እንደሚገልጸው መሬት የመንግስት እና የሕዝብ ነው ይላል:: ነገርግን መሬት የሕዝብ ነው፣ የመንግስት ነው፣ የሁለቱም ነው? መሬት የማንም አይደለም:: መሬት የገዢ ባለስልጣኖች የግል ንብረት ነው::

እንደፈለገ የሚሸጡት፣ የሚለውጡት፣ ጓደኛ የሚያፈሩበት፣ በዘመድ አዝማድ የሚያከፋፍሉት፣ ለወገን እያሉ ለነሱ ፓርቲ አባላት መመልመያ የሚጠቀሙበት ማማለያ ነው መሬት::

*መሬት የተማረውን ሳይቀር፡ ምሁሩን ሳይቀር ማሳወርያ ሆኗል። ዛሬ ምሁሩን አንዳንድ ቦታ በአበዛኛው በምንመለከትበት ጊዜ ስለፍትሕ፣ ስለመብት፣ ስለ እኩልነት የማያወራበት ጊዜ ደርሷል።ምክንያቱ ይኼ ማሳወርያ ነው ዛሬ በየከተማው እና በአዲስ አበባ ዙርያና ሌሎች ከተሞች አካባቢ በብዛት መሬት እየተሰጣችው አፋቸው ተሸብቧል።ስለዚህ መሬት አፍ መሸበቢያ ነው።

* መሬት ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል ውጭ የሚኖረውን ኢትዮጵያዊ መሳቢያ ማግኔት ሆኗል። ዳያስፖራ እየተባለ በአንድ ወቅት ግር... ብለው መጥተው፣ እዚህ ወገኖቻችን ሜዳ ላይ ወድቀው አንዲት ስንዝር መሬት የሌላቸው ወገኖች እያሉ በውጭ ቢያንስ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች መጥተው መሬት ተቀራምተው ሽጠውት ሄደዋል። ስለዚህ ማግኔት ነው የምንለው ለዚህ ነው።
*መሬት ዛሬ ጥቂቶች በብርሀን ፍጥነት ተዝቆ ወደማያልቅ ሀብት የተመነጠቁበት መንኮራኩር ነው።
ብንመለከት፣ እነድውም አንዳንዶቹን ሀብታሞች ብንጠይቃቸው... በሕዝቡ ዘንድ "ታሪኬ በአጭሩ" እየተባሉ የሚጠሩ አሉ። "እንዴት ነው፣ ይህ ሀብት ከየት መጣ እንዴት አገኛችሁ?" ተብለው ቢጠየቁ "እንደዚህ አድርጌ፣ እንደዚህ ለፍቼ አመጣሁ..." ማለት እንኳ የማይችሉ፣ገንዘቡን እንዴት እንዳፈሩት የማያውቁ...ስለዚህ ዛሬ መሬት እንደዚህ ነው:: መሬት የምንም አይደለም
መሬት ወሳኝ ሀብት መሆኑን እናውቃለን::
እኛ ኢትዮጵያዊያን ከዚህ ሀብት ጋራ ባለን ግንኙነት ምክንያት የዜገነት ደረጃችን በ4 ቦታ የተከፈለ ይመስለኛል:-->

1.መሬቱን የሚሸጡ አሉ አንደኛ ደረጃ ዜጎች
2.መሬቱን ከነሱ የሚቀበሉ አሉ፣ ሁለተኛ ደረጃ ዜጎች

3.እነሱ ሲቀባበሉ ቁጭ ብሎ ትዕይንቱን የሚመለከተ ዜጋ ደግሞ አለ ፤ ሦስተኛ ደረጃ- የበይ ተመልካች
4.መሬቱን ተነጥቆ፣ እትብቱ ከተቀበረበት፣ ተወልዶ ካደገበት መሬቱ ሥፍራ እየተባረረ መሬቱ ለሌላ የሚሰጥ የዚህ ድርጊት ሰለባ የሆነ አርሶ አደር ደግሞ አለ::

እኛ ምንታገለው ለዚህ ነው!!!

*****ደግማችሁ ደጋግማችሁ አድምጡት፣ የተቃውሞው መሠረታዊ ጥያቄዎች ያልገባችሁ ፍንትው ይልላችኋል። ይህ የጭቁን ኢትዮጵያዊያን ጥያቄ ነው!
የመንግሥት ኃይሎች ኦሮሚያ ውስጥ እየወሰዱ ያሉት እርምጃ “እጅግ አስከፊ” ወይም በእንግሊዝኛው ቀጥተኛ አባባል “ብሩታል” ናቸው ሲል ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አውግዟል

Sunday, October 18, 2015

BREAKING NEWS

BREAKING NEWS

**********************

The public meeting convened by Oromo Federalist Congress (OFC) in Finfinne Sunday, October 18, to discuss the so-called Addis Ababa and Oromia Special Zone Integrated Development Master Plan has ended adopting a 9-point resolution expected to be announced by OFC in an official press release. Sources say the meeting concluded that the Master Plan is a land grab policy disguised as a development plan and called on Ethiopian authorities to halt it, and on the public to continue rejecting it.

Saturday, October 17, 2015

365 DAYS IN PRISON

ፍትሕና ልዕልና ጋዜጦች፣ እንዲሁም የፋክትና የአዲስ ታይምስ መፅሔቶች ባለቤትና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ከታሠረ ፤ ጥቅምት 3 ቀን 2008 ዓ.ም አንድ ዓመቱን ደፍኗል፡፡ የተመስገን ጤና አሳሳቢ መሆኑን ቤተሰቡቹ ገልጸዋል፡፡ ማረሚያ ቤቱ ግን ተመስገን ሕክምና እያገኘ መሆኑን ጤናማም እንደሆነ ይናገራል፡፡

የተመስገን ደሣለኝ ታናሽ ወንድም ታሪኩ ደሣለኝ ተመስገንን ረቡዕ፤ ጥቅምት 3 ቀን 2008 ዓ.ም ዝዋይ ሄዶ መጎብኘቱንና፣ ወንድሙ የግራ ጆሮው ሙሉ በሙሉ እንደማይሰማ፣ ጀርባው ላይ ያለው እብጠት እየባሰበት መሆኑን በጀርባው መተኛትም እንደማይችል አስረድቷል፡፡
ተመስገን ማረሚያ ቤቱ ውስጥ ሕክምና እንደማያገኝና ቤተሰቡም ለማሳከም ቢጠይቅም ፍቃድ መነፈጉን፣ ጉዳዩን ወደ ፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ይዘው ሄደው “በማረሚያ ቤቱ ጉዳይ ጣልቃ አንገባም” የሚል መልስ ማግኘታቸውን ታሪኩ ለቪኦኤ ገልጿል፡፡
ተመስገን ያዘጋጃቸው ከነበሩት መፅሔቶች በአንዱ ላይ አምደኛ የነበሩት የሕግ ባለሙያ ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያምም ከጥቂት ወራት በፊት ከፕሮፌሰር መስፍንና ከሌሎች ሁለት ሰዎች ጋር ሆነው እዚያው ዝዋይ ድረስ ሄደው እንዳዩትና በወቅቱ የግራ ጆሮው ይደማ እንደነበር ገልፀዋል፡፡
የተመስገን ደሣለኝ ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንንም የዛሬ ሦስት ወር አካባቢ ዝዋይ ሄደው ያዩት መሆናቸውንና በቦታው ርቀት ምክንያት ከዚያ በኋላ በአካል እንዳላገኙት ገልፀው ከቤተሰቦቹ ግን አሁን ያለበትን ሁኔታ እንደሚያውቁ ተናግረዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሕገመንግሥት፣ መንግሥቱ ባወጣቸው ደንቦችና በዓለምአቀፍ ድንጋጌዎችም መሠረት ማንም እሥረኛ ጤንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ መያዝ እንደሚገባው፤ አስፈላጊ በሆነ ጊዜም ሕክምና የማግኘት መብት እንዳለው፤ የማረሚያ ቤቱ አስተዳደርም ሆነ የወህኒ ቤቱ ሃኪም ታራሚው ሕክምና ማግኘቱን የማረጋገጥ ግዴታ እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡
ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ የማረሚያ ቤቱ የፅሕፈት ቤት ኃላፊ ተመስገን አዲስ አበባ ድረስ ተወስዶ ሕክምና ማግኘቱን፤ በማረሚያ ቤቱ ውስጥም እየታከመ መሆኑን፣ ጤናማና እየተንቀሣቀሰ ያለ መሆኑን ገልፀው ጤንነቱ ታውኳል፤ ሕክምና ማግኘት አልቻለም የተባለው ሃሰት መሆኑን ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ተናግረዋል፡፡
ጠበቃው አቶ አምሃ ግን አዲስ አበባ ድረስ ሄዶ አለመታከሙን፣ ሄዶ ቢሆን ኖሮ እርሣቸው ያውቁ እንደነበር ተናግረዋ የማረሚያ ቤቱን የሥራ ኃላፊ መግለጫ አስተባብለዋል፡፡
 

Friday, September 11, 2015

በ2008 ወንድሞቻችን፣እህቶቻችንና ኢትዮጵያ ነፃ የሚወጡበት አመት !!!

በ2008 ወንድሞቻችን፣እህቶቻችንና ኢትዮጵያ
ነፃ የሚወጡበት :የኢትዮጵያ ህዝብየ24ዓመቱን የህወሀት አገዛዝ በቃህ የሚልበት:አመት
 

Sunday, September 6, 2015

የህወሀት እስርና እንግልት ያልበገረው ፍቅር





የህወሀት እስርና እንግልት ያልበገረው ፍቅር

ቂሊንጦ የተካሄደው የቀለበት ስነስርዓት





ብዙ ጊዜ ስለተቃራኒ ፆታ ፍቅር መጻፍ ብዙመ አልወድም ወይም አይመቸኝም ይህ ተከታዩን በቂሊንጦ እስር ቤት ከሰሞኑ የተፈፀመው የቀለበት ስነስርዓት ስሠማ ግን የሆነ የተለየ ነገር ሆኖ ስላገኘሁት ትንሽ ፈለግኩኝ፡፡

ጉዳዩ እንዲህ ነው በተደጋጋሚ ከዚህ ቀደም እዚህ ፌስቡክ ላይ እንደገለፅኩት በአንድ ወቅት የአሁኑ የኢትዮጵያ አየር ሐይል አባል የነበረው ወጣት ሻለቃ አክሊሉ መዘነ የገዢውን ፓርቲ ዘረኝነት እና ጭቆና መቋቋም አቃተኝ በማለት የኢትዮጵያ አየር ሀይልን ከድቶ ኤርትራ በመግባት የትጥቅ ትግል እያካሄደ የሚገኘውን አርበኞች ግንቦት 7 ህዝባዊ ሐይልን ይቀላቀላል ወጣቱ የአየር ሐይል አባል ወደአርበኞች ግንቦት 7 መቀላቀሉን የሠሙት የገዢው ፓርቲ ደህንነቶች በቂም በቀል ተነሳስተው የሻለቃ መዘነ ታናሽ ወንድምን ሠይፈ መዘነን ከሚኖርበት ኮተቤ አካባቢ በመያዝ ወደማዕከላዊ በመውሰድ ከፍተኛ ድብደባ የፈፀሙበት ሲሆን በወቅቱም ይህንን ጉዳይ መረጃ አሰባስቤ ይፋ ማውጣቴ ይታወሳል፡፡ እናም ታናሽ ወንድምዬወን ሠይፈ መዘነን ማዕከላዊ ወስደው ከደበደቡት በኋላ ፍርድ ቤት እንኳን ሳይወስዱ በአሁኑ ሠዓት ቂሊንጦ ወስደው አስረውት ይገኛል አስገራሚው ነገር ሠይፈ መዘነ ከጉዳዩ ጋር ምንም አይነት ግኑኝነት የሌለውና ምንም አይነት ፖለቲካዊ ተሳትፎ ያልነበረውና ስለጉዳዩ ምንም ሳያውቅ በግል ስራ ይተዳደር የነበረ ወጣት ነው፡፡

የሠይፈ መዘነን ወደቂሊንጦ እስር ቤት መዛወር የሠማችው ፍቅረኛው ሚዛን ፎቶው ላይ የምንመለከታት እንስት ጓደኞቿን ሰብስባ ቂሊንጦ እስር ቤት ድረስ በመሄድ ለፍቅረኛዋ ለሠይፈ መዘነ የቃልኪዳን ቀለበት አድርጋለታለች፡፡ በዙሪያዋ የሚገኙ ወጣቶች ሰይፈ በቃ ሻለቃው ወንድሙ አክሊሉ ከድቶ ኤርትራ በመግባቱ የህወሀት ሠዎች ለቂም በቀል ሠይፈን ምን አልባት ለበርካታ አመታት ሊያስሩት ይችላሉ የሚል ማስፈራሪያ ቢሠጧትም አሉባልታውንና ማስፈራሪያውን ችላ ብላ ከሠሞኑ ለሠይፈ መዘነ ቀለበት አድርጋለት እንዲህ ብላው ከቂሊንጦ እስር ቤት ለቃ ሄዳለች ""እውነት ማሸነፏ አትቀርም ያኔ አንተ ነፃ ትወጣና የቃልኪዳን ቀለበታችንወደትዳር ቀለበትነት ትለወጣለች እስከዛው ግን እጠብቅሀለው እወድሀለው""

ምስሉ ላይ የምትመለከቷቸው በአሁኑ ሠዓት ቂሊንጦ በእስር ላይ የሚገኘውን ሠይፈ መዘነን እና ፍቅረኛውን ሚዛንን ነው

Ermias Tokuma Alemayehu 

Thursday, September 3, 2015

የአቶ ሃብታሙ የአቶ አብርሃም ሰሎሞን መለቀቅ ታገደ!!!

የቀድሞው አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ወጣት ሀብታሙ አያሌውና ሌሎች የፖለቲካ አመራሮች  ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንዲፈቱ የሰጠውን ትዕዛዝ የበታች ፍርድ ቤቱ አግዷል፡፡
ፍርድ ቤቱ ውሣኔውን የሰጠው የአቃቤ ሕግን አቤቱታ ተቀብሎ ነው፡፡
ጉዳዩ ያስቀርብ ወይም አያስቀርብ እንደሆነ ለማየትም ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ ሰጥቷል፡

Thursday, May 21, 2015

ህዝባዊ እምቢተኝነት ያብብ ይለምልም!




ለኢትዮጵያ ህዝብ በሙዚቃው በተላለፈው ጥሪ የ24ዓመቱን የህወሀት አገዛዝ በቃህ የሚልበት ጊዜው ዛሬ ሳይሆን አሁኑኑ ነውገዥው የወያኔ መንግስት ስልጣን ከያዘ ጀምሮ አምስተኛው የኢትዬጲያ ብሄራዊ ምርጫ ይካሄዳል ፡፡ ሶስተኛውና ተስፋ የፈነጠቀው አገራዊ ምርጫ ተስፋ አስቆራጭ በሆነ የፓለቲካ ምህዳር መዘጋት ከተጠናቀቀ በኋላ የተካሄደውን አራተኛው ምርጫ ኢህአዴግ 99.6 በመቶ የፓርላማ መቀመጫ “በማሸነፍ” ተቆጣጥሮታል፡፡ ከቀናት በኋላ የሚካሄደው አምስተኛ አገራዊ ምርጫ የፓለቲካ ምህዳሩን ለማሻሻል የሚረዳና መጠነኛ ክፍተት ሊፈጥር ይችላል ተብሎ ቢጠበቅም በተቃራኒው ገዥው ፓርቲ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በከፍተኛ ሁኔታ እያዳከመ ተቺዎችን እና ሌሎች ነጻ ድምጾችን ለእስር ዳርጎ በከፍተኛ ጫና ታጅቦ ይካሄዳል፡።በቅርቡ ከእስር የተለቀቁት አቶ በቀለ ገርባ በምርጫ ቅስቀሳ ላይ እያሉ ተደበደቡ። ዘረፋም ተፈጽሞባቸዋል። የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር ዶክተርመረራ ጉዲና መንግስት ምጥ ይዞታል። የህዝብ ማዕበል አስፈርቶታል። የለየለት ተናካሽ ወጥቶታል ይላሉ።
_ምርጫው ሲቃረብ አፈናው፡ እስሩ፡ ማሰቃየቱ፡ ማሳቀቁ፡ ግድያው በየአቅጣጫው በርትቷል። ሰማያዊ፡ መድረክና ሌሎች ፓርቲዎች አቤቱታቸውን እያቀረቡ ናቸው። በዚህ መሃል ዕቅድ ያልተያዘላቸው፡ በጀት ያልተመደበላቸው ፕሮጀክቶች መሰረተ ድንጋይ በየቦታው እየተጣለላቸው ነው። አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በዚህም የተነሳ ሰሞኑን ስራ በዝቶባቸዋል።
_አዲስ አብዮተኛ ሙዚቃ ሰሞኑን ለአድማጭ ጆሮ ደርሷል።
ለኢትዮጵያ ህዝብ በሙዚቃው በተላለፈው ጥሪ የ24ዓመቱን የህወሀት አገዛዝ በቃህ የሚልበት ጊዜው ዛሬ ሳይሆን አሁኑኑ ነው!!!

Thursday, April 30, 2015

ኢትዮጵያ በታሠሩ ጋዜጠኞች ብዛት በአፍሪካ አንደኛ ነች

Imprisonment is the most effective form of intimidation and harassment used against journalists.

 

"
ሃሣብን የመግለፅ ነፃነት መብቷን ተግባራዊ በማድረጓ ብቻ ታሥራ የምትገኘውን ርዕዮትን እንዲፈታ ለመንግሥቱ ጥሪያችንን እናቀርባለን - መንግሥቱ ፀረ-ሽብር አዋጁን ሃሣብን በነፃነት የመለዋወጥን ተግባር ለመጠምዘዝ ጉዳይ ከመጠቀም እንዲቆጠብም እናሳስባለን"FREE THE PRESS


Seven of the 10 most censored countries-Eritrea, Ethiopia, Azerbaijan, Vietnam, Iran, China, and Myanmar-are also among the top 10 worst jailers of journalists worldwide, according to CPJ's annual prison census


In Ethiopia--number four on CPJ's most censored list--the threat of imprisonment has contributed to a steep increase in the number of journalist exiles. Amid a broad crackdown on bloggers and independent publications in 2014, more than 30 journalists were forced to flee, CPJ research shows. Ethiopia's 2009 anti-terrorism law, which criminalizes any reporting that authorities deem to "encourage" or "provide moral support" to banned groups, has been levied against many of the 17 journalists in jail there.


How censorship works: As Ethiopia prepared for its May 2015 elections, the state systematically cracked down on the country's remaining independent publications through the arrests of journalists and intimidation of printing and distribution companies. Filing lawsuits against editors and forcing publishers to cease production have left only a handful of independent publications in a country of more than 90 million people. Ten independent journalists and bloggers were imprisoned in 2014; authorities filed a lawsuit in August accusing six publications of "encouraging terrorism," forcing at least 16 journalists to flee into exile. There are no independent broadcasters, though broadcasts from the U.S.-based opposition Ethiopian Satellite Television (ESAT) intermittently air within the country. The state-controlled telecommunications company Ethio Telecom is the sole Internet provider and routinely suspends critical news websites. International journalists work in Ethiopia, but many are under surveillance and face harassment. Although journalists have not had difficulties acquiring accreditation in the past, newer arrivals say that they face challenges.


Lowlight: Authorities in 2014 unleashed the largest onslaught against the press since a crackdown in 2005 after disputed parliamentary elections. Ten independent journalists and bloggers were arrested on anti-state charges, and at least eight independent publications were shut down.


https://cpj.org/2015/04/10-most-censored-countries.php

Friday, April 17, 2015

በኢትዮጵያ የሚታየው የህንጻ ግንባታ የድህነት መሸፈኛ ጭምብል ይሆንን?(Is Ethiopia's building boom masking poverty?


 Is Ethiopia's building boom masking poverty?
Africa blog: Is Ethiopia's building boom masking poverty?

Whenever we set up our camera and flapped open our sun reflectors in Ethiopia's capital, Addis Ababa, passers-by became curious and eager to help.

But getting them to talk on camera was another matter as in general residents of the city are reticent and keep their views to themselves.

We were filming in Addis Ababa for a programme charting the changes in the country, yet it was only on the flight back to South Africa that I met an Ethiopian willing to be candid.

I found myself seated next to an inquisitive elderly Ethiopian woman, who was chatty despite the early morning departure.

However, she was not so open as to be willing for me to mention her name here.

She wore a green twin-set, leggings and woollen socks with her loafers. After the rigorous security checks, she took the socks off, saying she only wears them to keep her feet clean at the end of the security protocols.

She reminded me a bit of my mother, both caring and bossy all in one person.

During the flight, she cut me a portion of her fruit and insisted that I eat every morsel; her stern gaze suggested that I had no choice.
We talked about a lot of things, including my impressions of Nigeria, especially following the ground-breaking presidential election there when the incumbent lost.

She was proud of the manner in which Nigerians had used their vote to make a strong statement about their government.

I replied that perhaps if Ethiopians have strong views about the ruling party - the EPRDF, in power since 1991 - then they could also do the same when elections are held in May. 
http://www.bbc.com/news/world-africa-32310735

Friday, February 6, 2015

የዞን ዘጠኝ ተከሣሾች የመሃል ዳኛው እንዲቀየሩ ጠየቁ!

የዞን ዘጠኝ ጋዜጠኞችና የኢንተርኔት ፀሐፊዎች

እሥር ቤት ውስጥ የሚገኙት ዘጠኝ ጋዜጠኞችና የኢንተርኔት ፀሐፍት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ሰብሳቢ ዳኛ ከዚህ በኋላ ጉዳያቸውን እንዳይመለከቱ ያቀረቡት አቤቱታ ውድቅ ተደርጓል፡፡
አቤቱታ ያቀረቡባቸው ዳኛ ግን በራሣቸው ፈቃድ ጉዳዩን ላለማየት መወሰናቸውን ገልፀዋል።
 
ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ
የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ጋዜጠኞችን ጉዳይ የሚመለከተው የልደታው ችሎት ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚሰጠው ውሳኔ ምን ሊሆን እንደሚችል በጉጉት ሲጠበቅ ነበር። በተለይም ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞቹ የመሃል ዳኛው ስራቸውን በሚገባ እያከናወኑ ስላልሆነ፤ እንዲነሱላቸው ነበር በደብዳቤ የጠየቁትከተከሳሾቹ አንዱ አቤል ዋበላ እሥር ቤት ውስጥ ግፍ እንደተፈፀመበት ለፍርድ ቤቱ አቤት ብሎ መፍትሔ እንዲሰጠው አመልክቷል፡አቤል ዋበላ እንደትላንት ከፍርድ ቤቱ ወደ ቅሊንጦ ማረሚያ ቤት ሲወሰድ፤ ፖሊሶቹ እረስተው በእጁ ካቴና ሳያስገቡ ቀርተው ነበር። ያለካቴና ቅሊንጦ ከደረሰ በኋላ ግን የደረሰበትን ስቃይ ሲያስረዳ በፍርድ ቤቱ ውስጥ የተገኙት በሙሉ አዝነው ነበር። “ቅሊንጦ ስንደርስ እጄ ላይ ካቴና ስላልነበረ፤ የማረሚያ ቤቱ ሰራተኞች እየሰደቡ እና እያንገላቱ እጄን በውሻ ሰንሰለት አስረው ነው ያሳደሩኝ” በማለት እንባ እየተናነቀው ነበር የተናገረው። “ሌላው ቀርቶ ማዕከላዊ እያለሁ በደረሰብኝ ከፍተኛ ድብደባ ምክንያት አንድ ጆሮዬ በደንብ አይሰማም። በመሆኑም ለመስሚያ የሚያገለግለኝን የጆሮ ማዳመጫዬንም ወስደውብኛል” በማለት የደረሰበትን ግፍ እና በደል አስረድቷል።
ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለማየት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡