Thursday, November 29, 2012

አይኤልኦ ኢትዮጵያን ለሠራተኞች መብቶች "ክፉ" ሃገር ሲል ፈረጀ


አይኤልኦ ኢትዮጵያን ለሠራተኞች መብቶች "ክፉ" ሃገር ሲል ፈረጀ!!!

                                                                   
                                                                     

የአይኤልኦ አካል የሆነው የደራጀት ነፃነት ኮሚቴ ወደ 55 ዓመታት ለሚሆን ጊዜ በሥራ ላይ ያለ ተቋም ነው፡፡

ዛሬ 186 ሃገሮች የሥራ ድርጅቱ አባላት ሲሆኑ ዋና ዋና የሚባሉ ስምምነቶቹንና ሠነዶቹን በየሃገሮቻቸው የሕግ አውጭ አካላት አስፀድቀው ፈርመዋል፡፡ከእነዚህ ዋና ዋና እና ቁልፍ ከሚባሉ ስምምነቶች መካከል በማኅበር የመደራጀት ነፃነት ስምምነት፣ ለመደራጀት መብት የሚሰጥ ጥበቃ ስምምነት፣ የወል ድርድር መብት ስምምነት የሚጠቀሱ ሲሆን ኢትዮጵያም እነዚህንና ሌሎቹንም ስምምነቶች ተቀብላ ፈርማቸዋለች፡፡
ፕሮፌሰር ፖል ፋን ደር ሃይደን - የአ
በመሆኑም ኢትዮጵያ ስምምነቶቹን የማክበር ግዴታ እንደሚጠበቅባት የአይኤልኦ የመደራጀት ነፃነት ኮሚቴው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ፖል ፋን ደር ሃይደን ገልፀዋል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት የሥራ ድርጅት - አይኤልኦ ኢትዮጵያን የሠራተኛ መብት የማያከብሩ ክፉ ሃገሮች ዝርዝር ውስጥ ያሠፈረበት ድምዳሜ ላይ የደረሱት ኮሚቴአቸው የእነዚያን ስምምነቶች መጣስን የሚመለከቱ ስሞታዎችን የሚመረምር በመሆኑና እንዲህ ዓይነት አቤቱታዎችም ከኢትዮጵያ የደረሱት በመሆኑ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡


source <VoA Amharic
        <<<VOAAmharic

Wednesday, November 28, 2012

ሕዝቡ ከማጉረምረም አልፎ ንዴቱን በእንቅስቃሴ ለማሳየት ዝግጁ የሆነ አይመስልም”


ሕዝቡ ከማጉረምረም አልፎ ንዴቱን በእንቅስቃሴ ለማሳየት ዝግጁ የሆነ አይመስልም”

                       ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር
           
       



              ኢሕአዴግ ለሕዝብ ደንታ የለውም አሉ!

ባለፈው እሑድ ኅዳር 16 ቀን 2005 ዓ.ም. አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ በአገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ባደረገው ውይይት ላይ የመነሻ ሐሳብ ያቀረቡት የፓርቲው ሊቀመንበር ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሶተኛና በማጉረምረም ደረጃ ላይ የሚገኝ እንጂ፣ ንዴቱን በእንቅስቃሴ ለማሳየት ዝግጁ የሆነበት ደረጃ ላይ የደረሰ አይመስልም አሉ፡፡

የአገሪቱን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ በዳሰሱበት ክፍል ላይ በሰጡት ማብራሪያ ሕዝቡ በርካታ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንዳሉበት ገልጸው፣ ይህንን ሰቆቃውንና ብሶቱን ያማርራል እንጂ በይፋና በአደባባይ አይገልጽም ብለዋል፡፡ “ብሶቱ በማጉረምረም ደረጃ የሚገለጽ ነው እንጂ ወደ ኅብረተሰባዊ ንዴት አልተለወጠም ብለው፣” የተናጠል ንዴቶች አልፎ አልፎ ቢገለጹም ሰፊና የአጠቃላይ ኅብረተሰቡ አለመሆናቸውን አመልክተዋል፡፡

“እነዚህ የተናጠል ትናንሽ ንዴቶች ወደተደራጀና ሕዝባዊ የእምቢተኝነት እንቅስቃሴዎች አልተለወጡም፡፡ በሌሎች አገሮች በዳቦ ወይም በነዳጅ ዋጋ ላይ ትንሽ ጭማሪ ከታየ የኅብረተሰቡ ንዴት ይገነፍላል፡፡ በእኛ ሕዝብ ዘንድ ግን ይህ አይታይም፡፡ ምልክቶች ከታዩ ጥቂት፣ የተናጠል፣ ያልተደራጁና ያልተቀናጁ ናቸው፤” ብለዋል፡፡

ዶክተር ነጋሶ ገዥው ፓርቲ አምባገነን መሆኑን ባሰፈሩበት ክፍል፣ ኢሕአዴግ ለሕዝብ ደንታ የሌለው ድርጅት መሆኑን ገልጸው፣ የሕዝብን ፍላጎት አያዳምጥም ሲሉ ወቅሰዋል፡፡ “ሕዝብ እሱን ብቻ መስሎ እንዲያድር ነው የሚፈልገው፡፡ ከአገርና ከሕዝብ ይልቅ ፓርቲውን ያስቀድማል፡፡ በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጡትንና በአንቀጽ 29፣ 30፣ 31 እና 38 የተዘረዘሩትን መብቶች አፍኗል፤” ካሉ በኋላ፣ ተቃዋሚዎችን ለማጥቃት ብሎ ሕጎችን በማውጣት ሕግ አስከብራለሁ በማለት ሰብዓዊ መብቶችን እንደሚጥስ አስታውቀዋል፡፡

ኢሕአዴግ ዲሞክራሲያዊ ተቋማት እንዳይኖሩ አድርጎአል ብለው ሦስቱ የመንግሥት አካላት የሕዝብ አገልጋዮች ሳይሆኑ የፓርቲው መሣርያ ሆነዋል ብለዋል፡፡ “ገዥው ፓርቲ ሕገ መንግሥቱን አያከብርም፡፡ በሕገ መንግሥቱ የተከበሩ መብቶች ተግባራዊ ይሁኑ ሲባል አይፈቅድም፡፡ ሕገ መንግሥቱ የሚሻሻልበትን መንገድ ከመክፈት ይልቅ በሚያወጣቸው ሕጎች በእጅ አዙር ያሻሽላል፡፡ በአሠራሩ ሕገ መንግሥታዊ አስተሳሰብን ዋጋ አሳጥቷል፤” ሲሉ ወቅሰዋል፡፡

የመድበለ ፓርቲ ሥርዓቱን በገለጹበት ክፍል ደግሞ የፓርቲ ሥርዓቱ ዲሞክራሲያዊ አለመሆኑን አውስተው፣ በሕገ መንግሥቱ ቢደነገግም ዲሞክራሲያዊ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት በኢትዮጵያ የለም ብለዋል፡፡ በንጉሡ ዘመን በፓርቲ መደራጀት ክልክል መሆኑን፣ በደርግ የመጀመሪያ ዓመታት ለደርግ ታማኝ የሆኑ ለስሙ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ቢወለዱም በመጨረሻ አገሪቱ በአንድ ብቸኛ ፓርቲ (ኢሠፓ) ሥር መውደቋን፣ ኢሕአዴግ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ይመሠርታል ተብሎ ቢጠበቅም የአውራ ፓርቲ ሥርዓት መመሥረቱን ገልጸዋል፡፡

“ይህም አውራ ፓርቲነት እንደ አሜሪካና እንደ ታላቋ ብሪታኒያ ዴሞክራሲያዊ የሆኑ የሁለት ፓርቲዎች አውራነት ቢሆን ባልገረመን፣ ወይም እንደ ጃፓንና እንደ እስራኤል ዴሞክራሲያዊና መድበለ ፓርቲ ሥርዓት በሰፈነበት አውራ ሆኖ ቢመጣ እንቀበል ነበር፡፡ እርሱ ግን በአስገዳጅነት አንድ አውራ ፓርቲ ሆኖ ሌሎች ግን እንደ ጫጩት እንኳ እንዳይኖሩ በሙስና አሠራርና በልዩ ልዩ ተፅዕኖ ሥር ለማዳ ያደርጋቸዋል ብሎም ከነጭራሹ እንዲጠፉ ያደርጋል፤” ብለዋል፡፡

የምርጫ ሥርዓቱን ብልሹ ነው ያሉት ዶክተር ነጋሶ፣ የምርጫ ሥርዓቱ ለአገሪቱ ውስብስብ ሁኔታዎች ምቹ አለመሆኑን፣ በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች፣ ብዙ ሃይማኖቶችና የተለያዩ ርዕዮተ ዓለሞች ባሉበት አገር አሸናፊው ሁሉንም የሚወስድበት ሥርዓት እንደማይች አስረድተዋል፡፡ “ማኅበረሰባዊ ውክልና፣ ተጠያቂነትና የአሳታፊነት መርህን የተከተለ የተመጣጠነ ሥርዓት እንዲኖር አይፈለግም፡፡ ይባስ ብሎ በምርጫዎች መካከልና በምርጫዎች ወቅት ያለው የፖለቲካ ምኅዳር የተስተካከለ አይደለም፡፡ ዲሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊና ነፃነት የተሟላበት አይደለም፡፡ በዚህ የምርጫ ሥርዓት ውስጥ ተሸናፊ ፓርቲዎችን የሚመርጥ ብዙ ሚሊዮን የሕዝብ ክፍል በፓርላማ ደረጃ ድምፅ አልባ ይሆናል፤” ሲሉ በምሬት ገልጸዋል፡፡

ዶክተር ነጋሶ የፖለቲካ ልዩነቶችና ችግሮች የሚፈቱት በሰላማዊ መንገድ በውይይትና በድርድር ሳይሆን በጉልበት መሆኑን፣ የሕዝብ ወሳኝነት እንደማይፈለግ፣ ለሕዝብና ለአገር ጥቅም ሲባል ሰፊና አገራዊ የትብብር መድረክ ለመፍጠር ፈቃደኝነትና ዝግጁነቱ ደካማ መሆኑን ጠቅሰው፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች የተለመደው በአሸናፊነት የማንበርከክ ፍላጎትና የበላይነት ማስፈን አካሄድ በመሆኑ እምቢ ከተባለ ደግሞ ለማጥፋት መንቀሳቀስ መኖሩን አውስተዋል፡፡ ሰላማዊ የትግል ስልቶችን መጠቀም አለመጀመሩን ገልጸው ሰላማዊ ትግል ኃይል አልባ፣ ሕጋዊ፣ ሕገ መንግሥታዊና ዲሞክራሲያዊ በመሆኑ፣ አንዳንድ ሕጎችና ተቋማት የሌሎችን መብቶች የሚነኩ ከሆነ እምቢ ማለትና ያለመታዘዝን እንደሚያካትት ጠቁመዋል፡፡ “ሰላማዊ ትግል የተቃውሞ መሣርያ እንጂ የአመፅ መሣርያ አይደለም፤” ብለው፣ ሰላማዊ ትግል ሰፊ የመደራጀትና የዝግጅት ሥራ ይጠይቃል ብለዋል፡፡

የወደፊት የትግል አቅጣጫ ምን መሆን እንዳለበት ሲገልጹ፣ ሕዝብን ለለውጥ እንዲንቀሳቀስ ማድረግ፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን መሥራትና በሕዝብ ውስጥ የማደራጀትና የማቀናጀት ሥራዎች መሠራት አለባቸው ብለዋል፡፡ ገዥውን ፓርቲ ለለውጥ በማስገደድ ሰፊ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ መጀመር እንዳለበት አስረድተዋል፡፡ ብልሹ ያሉትን የፓርቲ ሥርዓት በመለወጥ የፖለቲካ ምኅዳሩ እንዲስተካከል በቁርጠኝነት ትግል መደረግ አለበት ሲሉ አመልክተዋል፡፡

“በአገራችን ለችግሮች መፍትሔ ለማፈላለግ ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ እርቅ መፍጠር አስፈላጊ ነው፡፡ የፖለቲካ ልዩነቶችን ወይም ችግሮችን ለመፍታት አንድነት በፕሮግራሙ ያስቀመጠው አቅጣጫ ትክክል ነው፡፡ ስለሆነም ችግሮችን በሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ መንገድ በውይይትና በድርድር የመፍታትን ባህል የበለጠ ማዳበር የትግላችን አቅጣጫ መሆን አለበት፤” በማለትና አንዳንድ ነጥቦችን በማከል ዳሰሳቸውን ደምድመዋል፡፡
 source << ሪፖርተር

Sunday, November 25, 2012

በሽብርተኝነት የተከሰሱ 29 ተጠርጣሪዎች በነፃ እንዲሰናበቱ ተጠየቀ


በሽብርተኝነት የተከሰሱ 29 ተጠርጣሪዎች በነፃ እንዲሰናበቱ ተጠየቀ


በዕለቱ ከፍርድ ቤቱ አጥር ውጭ በርካታ ሰዎች የተሰባሰቡ ቢሆንም ወደ ውስጥ መግባት አልቻሉም!

የሽብር ድርጊቶችን በመፈጸም፣ ሕገ መንግሥቱንና መንግሥታዊ ሥርዓቱን በማፈራረስ ሙከራ ወንጀልና ለሽብርተኝነት ድጋፍ በመስጠት ወንጀል ተጠርጥረው በፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ክስ የተመሠረተባቸው 29 ግለሰቦችና ሁለት ድርጅቶች፣ የተከሰሱት ሕገ መንግሥቱን ጥሶ በወጣ ወይም በሚቃረን ሕግ በመሆኑ በነፃ እንዲሰናበቱ ጠበቆቻቸው ጠየቁ፡፡ ከሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ባለቤት ተጠርጣሪ ወይዘሮ ሐቢባ መሐመድ መሐሙድ በስተቀር፣ ሁሉም ተጠርጣሪዎች በጋራ አሥር ጠበቆችን ያቆሙ ሲሆን፣ ክሱን እየመረመረው ለሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ የወንጀል ችሎት የክስ መቃወሚያ ሐሳባቸውን ኅዳር 13 ቀን 2005 ዓ.ም. አቅርበዋል፡፡ 

ፍርድ ቤቱ ተከፋፍለው የቀረቡትን አራት ክሶች በንባብ አሰምቶ እንደጨረሰ፣ የተጠርጣሪዎቹ ተከሳሾች የመጀመሪያ መቃወሚያቸውን አቅርበዋል፡፡ በወንጀል ሕጉ 130 እና በአዋጅ ቁጥር 25/88 መሠረት በቀረበው መቃወሚያ ላይ ጠበቆቹ እንዳብራሩት ከሕገ መንግሥቱ ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈጻሚነት አይኖረውም፡፡ ከሕገ መንግሥቱ ጋር እኩል ደረጃ ኖሯቸው አንድ አካል ተደርገው በሥራ ላይ ይውላሉ የተባሉት ኢትዮጵያ ፈርማ የተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶችና ሰነዶች ናቸው፡፡ እነዚህም በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ውስጥ ቁጥር 217ኤ (11) ላይ የፀደቀው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ፣ እ.ኤ.አ ዲሴምበር 16 ቀን 1966 ፀድቆ እ.ኤ.አ ማርች 23 ቀን 1976 በሥራ ላይ የዋለው የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳንና ጭካኔ የተሞላባቸው ኢ-ሰብዓዊና አዋራጅ አያያዞችንና ቅጣቶችን ለማስቀረት የተደረጉ ስምምነቶች እንደሚገኙ በተቃውሟቸው ጠቁመዋል፡፡ እንደጠበቆቹ ገለጻ፣ አዋጅ ቁጥር 652/2001 ከሕገ መንግሥቱና ከዓለም አቀፍ ስምምነቶች ጋር ይቃረናል፡፡ 

ጠበቆቹ አዋጅ 652/2001 እንዴት ሕገ መንግሥቱ እንደሚቃረን ለፍርድ ቤቱ ሲያስረዱ፣ በሕገ መንግሥቱ የአንድ ሰው የመኖሪያ ቤትና የግል ሕይወቱ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንደማይደፈር መደንገጉን ገልጸዋል፡፡ ያለ ሕግ አግባብና ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ አንድ በርባሪ ፖሊስ የግለሰብ ቤት መሄድ የማይችል መሆኑን ብቻ ሳይሆን፣ የተጠርጣሪው ግለሰብ ቤተሰቦች ወይም አባላት ከሌሉ፣ በሕጋዊ መንገድ ለብርበራ የተሰጠውን ትዕዛዝ ትቶ እንደሚመለስ በሕገ መንግሥቱ መደንገጉን አስረድተዋል፡፡ ፍርድ ቤትም ቢሆን የብርበራ ፈቃድ ሲሰጥ የግለሰቡን የግል ሕይወት ለመድፈር የሚያስችል መብት እንደማይሰጥም ጠቁመዋል፡፡ በተቃራኒ በድብቅ መረጃ መሰብሰብን የሚፈቅደው አዋጅ 652/2001 አንቀጽ 18 ሕገ መንግሥቱንና የሰውን ክብር እንደሚቃረንም አስረድተዋል፡፡ 

ጠበቆቹ በደንበኞቻቸው ላይ የቀረበውን ክስና የተጠቀሰባቸውን የፀረ ሽብር ሕግን፣ ከሕግ አውጭው ፓርላማ ጀምረው ይቃረናል እስካሉት ሕገ መንግሥት ድረስ እንዴት እንደሚቃረን ሲያስረዱ ከዓቃቤ ሕግና ከፍርድ ቤቱ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ጠበቆቹ በክሱ ላይ ብቻ አተኩረው መቃወሚያቸውን እንዲያቀርቡ በተደደጋሚ ከመናገሩም በተጨማሪ፣ ዓቃቤያነ ሕጉም ከመቀመጫቸው በተደጋጋሚ በመነሳት ጠበቆቹ የሚያቀርቡት መቃወሚያ ከሕጉ ውጭ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ እንዲያስቆምላቸው ጠይቀዋል፡፡ ጠበቆቹ በበኩላቸው፣ ተከሳሾች በቀረበባቸው ክስ ላይ መቃወሚያ ሲያቀርቡ ዓቃቤ ሕግ ተቃውሞ ለማቅረብ የሚያስችለው የሕግ ሥነ ሥርዓት ስለሌለ፣ በተደጋጋሚ እየተነሳ ተቃውሟቸውን ማስተጓጐል እንዲያቆም እንዲታዘዝላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡ 

ጠበቆቹ ክሱን የሚቃወሙበትን ሐሳብ ቀጥለው ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ በደንበኞቻቸው ላይ የተጠቀሰውና በዋናነት ክስ የተመሠረተበት የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ የማንንም ዜጋ ቤት መበርበርንና መድፈርን ብቻ ሳይሆን፣ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መያዝንና ማሰርን፣ ከፍርድ በፊት ንፁህ ሆኖ የመገመትን፣ በሕግ ፊት እኩል ሆኖ የመታየት መብትን በመደምሰስ ሕገ መንግሥቱን እንደሚቃረን አስረድተዋል፡፡ 

ደንበኞቻቸው ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተይዘው፣ ታስረውና ከሕግ አግባብ ውጭ ምርመራ ተፈጽሞባቸው፣ ከሕግ ውጭ በተገኘ ማስረጃ ተከሰው ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ጠበቆቹ ገልጸዋል፡፡ ደንበኞቻቸው ሕገ መንግሥታዊ ጥበቃቸውን የሻረውና የነጠቃቸው ሕገ መንግሥቱን ጥሶ የወጣው አዋጅ ቁጥር 652/2001 ሰለባ ሆነው እንጂ፣ ምንም ያላጠፉና የተከበሩ አባቶች፣ ምሁራን፣ የአገር ሽማግሌዎችና ለሁሉም ዜጋ በአርዓያነት ሊወሰዱ የሚችሎ ዜጎች መሆናቸውን አውስተዋል፡፡ የፀረ ሽብር ሕጉ ሕገ መንግሥቱን በመቃረኑ ተፈጻሚ ስለማይሆን ደንበኞቻቸው በነፃ እንዲሰናበቱ ጠይቀዋል፡፡   

ሌላው የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች ያነሱት ተቃውሞ፣ በተከሳሾቹ ላይ የተጠቀሰው የፀረ ሽብር ሕጉ አንቀጽ ሦስት የሚደነግገው ፍጻሜ ስላገኘ የሽብርተኝነት ድርጊት መሆኑን ጠቁመው፣ አንቀጽ አራት ደግሞ ፍጻሜ ስላላገኙ የሽብርተኝነት ድርጊቶች መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዓቃቤ ሕግ ደንበኞቻቸውን በአንቀጽ ሦስት የተከለከሉ የሽብርተኝነት ድርጊት ፈጽመዋል በሚል ከሷቸው ሳለ፣ በድጋሚ አንቀጽ አራትን በመጥቀስ በአንቀጽ ሦስት የጠቀሰውን ወንጀል ለመፈጸም በማቀዳቸው፣ በማሴራቸውና በመሰናዳታቸው መከሰስ አለባቸው ማለቱ ሕጋዊ አለመሆኑንና እንደማያስኬደው አስረድተዋል፡፡ ተፈጸመ በተባለው ጉዳት በምንና በማንኛውም ሁኔታ ጉዳቱን እንዳደረሱ ባልተገለጸበት ሁኔታ አንቀጽ 32(1)ሀን መጥቀስ አግባብ ባለመሆኑ ክሱ መሰረዝ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ 

ድርጊቶች ተፈጸሙ የተባለበት ቀንና የማነሳሳት ተግባር ተፈጸመ የተባለበት ጊዜ የተለያየ መሆኑን፣ በሰውና በንብረት ላይ ተፈጸመ በተባለው ወንጀል ላይ ቀጥታ ፈጻሚዎቹ እያሉ ደንበኞቻቸው አነሳስተዋል በሚል፣ የፈጸመው ማን እንደሆነ ሳይለይ ተለይቶ ባልቀረበበት ሁኔታ መከሰሳቸው አግባብ አለመሆኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡ ድርጊቱን ፈጽመዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች ተከሰው በቀላል እስራት ቅጣት ከተወሰነባቸው በኋላ፣ አነሳስተዋል የተባሉት ደንበኞቻቸውን በፀረ ሽብር ሕግ መክሰስ “ሁሉም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው” የሚለውን ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌና በወንጀል ሕጉ ላይ “የወንጀል ሕግ ልዩነት ሳያደርግ በሁሉም ላይ እኩል ተፈጻሚ ይሆናል” የሚለውን ድንጋጌ በግልጽ የሚቃረን መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ውድቅ እንዲደረግም ጠይቀዋል፡፡ 

ጠበቆቹ በመቃወሚያቸው ያነሱት ተቃውሞ በደንበኞቻቸው ላይ የቀረበው ክስ ተነጣጥሎ እንዲቀርብላቸው ነው፡፡ በተለይ በፀረ ሽብር ሕጉ አንቀጽ 3 እና 4 የተጠቀሱት አግባብ የክስ አቀራረብን በሚመለከት የወንጀል ሕግ 116 የሚያዘውን የሚጻረሩ መሆኑን ነው፡፡ የወንጀል ድርጊት ተፈጸመበት የተባለው ቦታና ጊዜ መሠረታዊ የሕግ ስህተት እንዳለበትም ጠቁመዋል፡፡ በክሱ ላይ ወሩ በውል ተለይቶ ካልታወቀበት 2001 ዓ.ም. ጀምሮ ከማለት ውጪ መቼና በማንኛው ቀን እንደሆነ አለመጠቀሱንም ተናግረዋል፡፡ ፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ የወጣው ወይም ሕግ ሆኖ የፀደቀው ነሐሴ 22 ቀን 2001 ዓ.ም. ነው፡፡ በመሆኑም ደንበኞቻቸው ሊከሰሱ የሚገባው ሕጉ ከወጣበት ከነሐሴ 22 ቀን 2001 ዓ.ም. ጀምሮ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህ መሠረት ተከሳሾቹ የሽብር ድርጊት ለመፈጸም ክሱ በህቡዕ የተደራጁት የፀረ ሽብር ሕጉ ከመውጣቱ በፊት ወይም ከወጣ በኋላ መሆኑን ዓቃቤ ሕግ ለይቶ ባላወቀበት ሁኔታ የቀረበባቸው በመሆኑ፣ በወንጀል ሕጉ 111 መሠረት ክሱ ውድቅ መደረግ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

ዓቃቤ ሕግ በክሱ ውስጥ ጅሀድ፣ የሃይማኖት አስተማሪዎች (የኡስታዞች ቡድን) የዳኢዎች ቡድን፣ አክራሪ አስተሳሰብና አስተምህሮት፣ አስተምህሮትን የሚሰብኩ የመገናኛ ብዙኃን፣ የሰደቃና የአንድነት ፕሮግራም፣ ወዘተ የሚሉ ለ1996 የወንጀል ሕግም ሆነ ለፀረ ሽብር አዋጁ ባዕድ የሆኑ ቃላትና ሐረጐችን በክሱ አላግባብ መጠቀሙን ጠበቆቹ ጠቁመዋል፡፡ የተጠቀሱት ቃላት ሐረጐች በሕግ አነጋገሮች ውስጥ የሌሉ ብቻ ሳይሆን ቃላቱ ሃይማኖታዊና ፖለቲካዊ በመሆናቸው ፖለቲከኞች ወይም ኢኮኖሚስቶች የሚጠቀሙባቸው መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡ ከፊሎቹም የዓረብኛ ቃላት መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ ዓቃቤ ሕግ በሁለተኛ ክሱ ያነሳቸው የክስ ነጥቦች እርስ በርስ የሚቃረኑ ለመሆናቸውም በዝርዝር አስረድተዋል፡፡

ተከሳሾቹ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማፈራረስ ሙከራ ማድረጋቸውን ዓቃቤ ሕግ በመጥቀስ ክስ የመሠረተባቸው፣ በአንዋር መስጊድ ለተሰበሰበው ሕዝብ የሚያነሳሱና በሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ ላይ አመኔታ የሚያሳጡ ንግግሮችና ጽሑፎችን ተጠቅመው፣ ለአመጽና ለሽብር ተግባር በማዘጋጀት ረብሻ አነሳስተዋል መባሉ እውነት ሆኖ ቢገኝ እንኳ፣ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው መሆኑን እንጂ ወንጀል መፈጸም አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ አንድን ሐሳብ የመያዝ ነፃነትን ቀርቶ መገለጹ እንኳን ገና ለገና የሚያመጣውን አደጋ መሠረት አድርጐ ሊገደብ እንደማይችል ወይም አይገደብም የሚለውን ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 29 የሰጠውን መብት የጣሰ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ሌላው ፍርድ ቤቱ በዕለቱ ያደመጠው የክስ መቃወሚያ፣ ለብቻቸው ጠበቃ ያቆሙትን የሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ባለቤት ወይዘሮ ሐቢባ መሐመድ መሐሙድን የክስ መቃወሚያ ነው፡፡ ወይዘሮ ሐቢባ በኦሮሚያ ክልል አስፋፍተዋል የተባለው አክራሪነት ምን ማለት እንደሆነ ዓቃቤ ሕግ በግልጽ አለማስረዳቱን፣ ከ28ቱ ተጠርጣሪዎች ጋር አብረው መከሰስ እንደሌለባቸውና ክሳቸውም ለብቻው ተነጥሎ እንዲቀርብ ጠበቃቸው ለፍርድ ቤቱ አመልክተዋል፡፡

ወይዘሮ ሐቢባ በኦሮሚያ ክልል አሠሩ የተባሉትን መስጅድ የእስልምና ጠቅላይ ምክር ቤት የሚያውቀውና ፈቃድ ያለው መሆኑን፣ ለሰደቃ የሚሆን ቁሳቁስ ይዘው ተገኝተዋል የተባለው ዓይነቱ እንዳልተጠቀሰና እሳቸውም ለሰደቃ የሚሆን ቁሳቁስ ይዘው አለመገኘታቸውን ጠበቃው አስረድተዋል፡፡ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸውም ጠይቀዋል፡፡

የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ያደመጠው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ የወንጀል ችሎት፣ ዓቃቢያነ ሕጉ በተቃውሞው ላይ ሐሳባቸውን እንዲያቀርቡ ጠይቋል፡፡ ዓቃቢያነ ሕጉ የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ሰፊ በመሆኑ ጊዜ ተሰጥቷቸው አስተያየታቸውን እንዲያቀርቡ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡ ጠበቆቹ ግን “ሕጉ የሚለው የክስ መቃወሚያ እንደቀረበ ወዲያውኑ ዓቃቤ ሕግ አስተያየት ይሰጣል ነው፡፡ በመሆኑም አሁኑኑ ምላሽ ወይም አስተያየት እንዲሰጥ ይታዘዝልን፤” በማለት በዓቃቤ ሕግ ላይ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል፡፡ 

ፍርድ ቤቱ ከተመካከረ በኋላ የክስ መቃወሚያ እንዳቀረበ ዓቃቤ ሕግ ወዲያውኑ አስተያየቱን ይስጥ የሚል የሕግ ሥነ ሥርዓት አለመኖሩን በመግለጽ፣ ዓቃቤ ሕግ ለኅዳር 21 ቀን 2005 ዓ.ም. አስተያየቱን እንዲያቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ችሎቱን አጠናቋል፡፡ 

በዕለቱ በነበረው ችሎት ከአንዳንድ የውጭ አገርና የአገር ውስጥ ጋዜጠኞች በስተቀር፣ የተከሳሾች ቤተሰቦችም ሆኑ ሌሎች ታዳሚዎች አልተገኙም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ችሎቱ ሞልቷል በመባሉ ነው፡፡ በዕለቱ ከፍርድ ቤቱ አጥር ውጭ በርካታ ሰዎች የተሰባሰቡ ቢሆንም ወደ ውስጥ መግባት አልቻሉም፡፡


Thursday, November 22, 2012

የእስክንድር ነጋ ጉዳይ ለተመድ ግብረኃይል ገባ


የእስክንድር ነጋ ጉዳይ ለተመድ ግብረኃይል ገባ


ለህሊና እስረኞች የሚሟገተው ፍሪደም ናው “Freedom Now” የሚባለው ድርጅት የእስክንድር ነጋን ጉዳይ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያላግባብ የታሠሩ ሰዎችን ጉዳይ ለሚያጠናው ግብረኃይል ማቅረቡ ታወቀ።
እስክንድር ነጋ
​​
ግብረኃይሉ በቀረበለት መመልከቻ ላይ በመጭው ሚያዝያ ውሣኔ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

Ethiopian Court Demands Justification for Journalist’s Conviction


Ethiopian Court Demands Justification for Journalist’s Conviction










Marthe Van Der Wolf  | VOA News
ADDIS ABABA — Ethiopia’s Federal Supreme Court has postponed hearing an appeal of the conviction of prominent Ethiopian journalist Eskinder Nega and opposition leader Andualem Arage.  But the court gave its first indication Thursday that charges brought by prosecutors under the Anti-Terrorism Proclamation may not be that strong by demanding that prosecutors justify the June convictions.
Journalist Eskinder Nega received an 18-year sentence, while opposition politician Andualem Arage is serving life in prison on terrorism-related charges.
Andualem’s lawyer, Abebe Guta, said the court has found many irregularities in the prosecution’s charges.
“As they scrutinized our ground of appeal they found so many legal and factual irregularities,” said Abebe. “Therefore, before the ruling passes, that means before our appeal is accepted or approved, they wanted to summon the prosecution officers to come and justify.”
Maran Turner, the executive director of Freedom Now, a Washington D.C.- based organization that works on individual prisoners of conscience cases, said the latest developments are positive. Freedom Now has been supporting Eskinder and brought his case before the United Nations Working Group on Arbitrary Detention.
“It seems to me that the court also is confounded by the charges against Eskinder and the other defendants,” Turner said. “So the fact that the court has postponed the case, it obviously acknowledges the flaws that we see, which is that the charges themselves are flawed. In fact, the case is flawed from the very beginning of arrest.”
Eskinder, Anualem and more than 20 others were found guilty of ties to a U.S.-based opposition group, Ginbot 7, classified as a terrorist organization by the Ethiopian government.
Amnesty International and other rights advocacy groups have said the trial was a sham used to silence dissent.
The prosecution will need to justify its convictions before the court on December 19.

    Sunday, November 18, 2012

    የጀርመኑ ድርጅት የኢትዮጵያ ቢሮውን ዘጋ!




    በጀርመናዊው የኖቤል ተሸላሚ በእውቁ ደራሲ ኤንሪሽ ቦል ስም የተመሠረተው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት በኢትዮጵያ ዲሞክራሲና ሰብዓዊ መብቶችን ለማበረታታት ሲያደርግ የቆየውን እንቅስቃሴ አቋርጦ ለመውጣት መገደዱን አስታውቋል።

    ኤንሪሽ ቦል ፋውንዴሽን ከኢትዮጵያ የሚወጣው በእንቅስቃሴዎቹ ላይ የተጣሉ ገደቦችን በመቃወም መሆኑን አስረድቷል።

    Saturday, November 17, 2012

    Norway refuses to grant Ethiopia’s fingerprint request of over 400 refugees

    SATURDAY, 17 NOVEMBER 2012 


    By Merga Yonas
    The Norwegian government has disagreed with Ethiopia on the latter's request for fingerprints of the over 400 Ethiopian refugees residing in Norway, who were expected to be deported, as it is not in their repatriation agreement. On January 26, Torgeir Larsen, Secretary of state with Norwegian government and Ambassador Berhane Gebrekristos, Minister of Foreign Affairs, signed a Memorandum of Understanding to repatriate back Ethiopian citizens in Norway. Since March 15, the Norwegian government was in the process of sending back over 400 Ethiopian refugees living in the country without legal documents or resident permits.

    Sources told the The Reporter that though the Ethiopian government requested as a precondition  fingerprints of the Ethiopians who are set to be deported, the Norwegian government refused to get engaged as the request was not in their repatriation agreement.

    The agreement was signed between the two countries to let citizens repatriate voluntarily, Ambassador Dina Mufti, spokesperson with the Ministry of Foreign Affairs told The Reporter. According to the agreement, the repatriation is going to be carred out by the Norwegian government.

    “Thus, we don’t follow up the status and I don’t have any information regarding the fingerprint request,” Dina told The Reporter.

    “In the first place there was no one who could voluntarily return back to Ethiopia, as many are political refuges and that is why the demonstration has kept on here in Norway,” an Ethiopian who resides in Norway told The Reporter in a telephone interview.

    The agreement stipulates that Ethiopian citizens, who choose to return voluntarily, are entitled to receive a lump sum upon arrival and will be offered support to reintegrate, which paves the way for a new start in Ethiopia. For Ethiopians, who do not want to go voluntarily, the Norwegian government will resort to the option of enforced return.

    A recent report from Norwegian Organization for Asylum Seekers (NOAS) shows that before the repatriation agreement was signed, the deportation of Ethiopians was very complicated. The number of deportations of Ethiopians from Norway and other Western countries in the past few years has been minimal. There have also been relatively few voluntary returns to Ethiopia.

    Thursday, November 15, 2012

    የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አዲስ አባላት

    መቀመጫው ጄኔቫ ለሆነው ምክር ቤት  ከተመረጡት አሥራ ስምንት ሃገሮች ብቃት ያላቸውና መመዘኛውን የሚያሟሉት አንድ ሦስተኛ ብቻ መሆናቸውን የመብቶች ተሟጋቾቹ ገልፀዋል፡፡

    ሂዩማን ራይትስ ዋች ከተመረጡት ሃገሮች መካከል ኢትዮጵያን አንስቶ በሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ከሚታወቁ ሃገሮች አንዷ እንደሆነች አመልክቷል፡፡ 

    አርባ ሰባት መቀመጫዎች ያሉት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አዘውትሮ የሚወቅሰው ለእሥራኤል ጉዳይ ልዩ ትኩረት ይሰጣል እየተባለ ነው፡፡ ከዚያ ጋር በሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ታሪካቸው ላይ እድፍ ብጤ አይጠፋቸውም የሚባሉ ሃገሮች አባላቱ የመሆናቸው ጉዳይም ሌላው ነቀፌታ የሚያደርስበት ነጥብ ነው፡፡ በምክር ቤቱ ውስጥ ያሉት መቀመጫዎች የሚደለደሉት በአካባቢያዊ የአመዳደብና የውክልና ሥርዓት ነው፡፡
    በዘንድሮው የምክር ቤቱ አባላት አሰያየም ላይ እውነተኛ ፉክክር የተካሄደው ከአምስት መቀመጫዎቹ ሦስቱን እንዲሞላ በተጠየቀውን “የምዕራብና ሌሎች” በሚባለው ምድብ ውስጥ ነው፡፡
    የሂዩማን ራይትስ ዋች የተባበሩት መንግሥታት ዳይሬክተር ፊሊፕ ቦሎፒዮን: የምክርቤቱ አባል ለመሆን ፉክክር ያለመኖሩና የሰብዓዊ መብቶች አያያዛቸው ጥያቄ ውስጥ የሆነ ሃገሮች አባል የመሆናቸው ጉዳይ ቅሬታን የሚያስነሣ መሆኑን በመጥቀስ ነቅፈዋል፡
    ቦሎፒዮን የኢትዮጵያን የመብቶች አያያዝ ታሪክ አንስተውም ወቅሰዋል፡፡

    “የኢትዮጵያ መንግሥት - አሉ ቦሎፒዮን - ይህንን አጋጣሚ ትርጉም ያላቸውን እርምጃዎች ለመውሰድ ሊጠቀምበት ይገባል፡፡ ለምሣሌ ሃሣብን በመግለፅና በመሰብሰብ ነፃነት፣ ወይም የፀጥታ ኃይሎቹን በተጠያቂነት በመያዝ፣ በተጨማሪም ምናልባትም አሁን እየተቀላቀለው ካለው የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ጋር በእውነተኝነት መተባበር መጀመር አለበት፡፡”







    Wednesday, November 14, 2012

    Ethiopia Freedom on the Net 2012


    INTRODUCTION: 

    Ethiopia is the second most populous country in Africa, but poor infrastructure and a government monopoly over the telecommunications sector have notably hindered the growth of information and communication technologies (ICTs). Consequently, Ethiopia has one of the lowest rates of internet and mobile telephone penetration on the continent. Despite low access, the government maintains a strict system of controls and is the only country in Sub-Saharan Africa to implement nationwide internet filtering.
    In 2011, in the wake of the Arab Spring protests in the Middle East and several online calls for similar demonstrations in Ethiopia,[1] the government reacted by strengthening internet censorship and carrying out a systematic crackdown on independent journalists, including at least one blogger. Beginning in June 2011, over ten journalists were sentenced to long prison terms,[2] mostly on questionable charges of terrorism. Among them was the editor of an exiled online news website who was sentenced in abstentia to life imprisonment. A prominent dissident blogger based in Ethiopia was also arrested in September 2011 and sentenced to 18 years in prison in July 2012.[3] The latest crackdown is part of a broader trend of growing repression against independent media since the 2005 parliamentary elections, in which opposition parties mustered a relatively strong showing.[4]
    Internet and mobile phone services were introduced in Ethiopia in 1997 and 1999, respectively.[5] In recent years, the government has attempted to increase access through the establishment of fiber-optic cables, satellite links, and mobile broadband services. It has refused to end exclusive control over the market by the state-owned Ethiopian Telecommunication Corporation (ETC). However, in December 2010 France Telecom took over management of ETC for a two-year period, renaming it Ethio Telecom in the process.[6] China has also emerged as a key investor and contractor in Ethiopia’s telecommunications sector.[7] Given allegations that the Chinese authorities have provided the Ethiopian government with technologies that can be used for political repression, such as surveillance cameras and satellite jamming equipment,[8] some observers fear that the Chinese may assist the authorities in developing more robust internet and mobile phone censorship and surveillance capacities in the coming years.

    Sunday, November 11, 2012

    Ethiopian Federal Police Raids Kemise Town, Conducting House-to-House Search

    Ethiopian Federal Police Raids Kemise Town, Conducting House-to-House Search








    Sunday, November 11, 2012

    Ethiopian Federal Police and armed government security forces have reportedly been mobilized to towns in South Wollo and Oromia Zones of the Amhara State late on Saturday. The town of Kemisse in Oromia Zone of the State is currently surrounded by Federal Police Forces.

    Reports from the town indicate that the federal police are carrying out house-to-house searches at the residences of several Muslims. 

    Kemise is one of the towns where weekly peaceful protests against government interference on Muslim religious affairs is being conducted every Friday. 

    It is to be recalled that a similar raid carried out by Federal Police Forces in Gerba town, South Wollo Zone of the Amhara State, on October 21st sparked clashes between the town’s Muslims and the police and led to the death of at least five civilians.

    Friday, November 2, 2012

    ህወሃት:የአየር ሃይል አዛዥ የሆኑትን ሜጀር ጄኔራል ሞላ ሃይለማርያምን ከስልጣን አነሳ !

    ህወሃት ኢህአዴግ የአየር ሃይል አዛዥ የሆኑትን ሜጀር ጄኔራል ሞላ ሃይለማርያምን ከስልጣን አነሳ !
    ሜጀር ጄኔራል ሞላ ከስልጣን መውረድ ህወሃት ውስጥ ከተፈጠረው መከፋፈል ጋር የተያያዘ ነው :: ሜጀር ጄኔራል ሞላ የአየር ሃይሉ አዛዥነት ስልጣን ጨብጠው ከነበሩት አራት የህወሃት አባላት ማለትም ከጄኔራል አበበ ተክለሃማኖት( ጆቤ) ጄኔራል መሃሪ ዘውዴ (ወዲ ዘውዴ) እና ጄኔራል አለምሸት ደግፌ አንዱ ነበረ ::
    ባሁኑ ጊዜ የቀድሞው አየር ሃይል አዛዥና የህወሃት አባል የሆነው እንዲሁም በዚህ አመት መጀመሪያ ላይ ጠቅላይ ሚንስትር በሌለበትና ፓርላማ ባልመከረበት ሁኔታ የወታደራዊ ማዕረግ እድገት ከተደረገላቸው የመከላከያ አባላት አንዱ የሆኑት ሜጄር ጄኔራል መሃሪ ዘውዴ (ወዲ ዘወዴ) አየር ሃይሉን ባዛዥነት እየመሩ እንደሆነ ታውቋል::

    The latest Victims are 9 members of the Oromo Federalist Congress,

    As expected the kangaroo court has passed 'terrorism' verdict against another set of Oromo political prisoners . The latest Victims are 9 members of the Oromo Federalist Congress, including senior leaders Bekele Garba and Olbana Lellisa. When the judge gave Mr Bekele Garba chance to seek reduction of sentence, Bekele reportedly said " In my entire life I fought for justice, democracy and equality, I have opposed discrimination. I was born Oromo not by my choice but of Gods will. I have am proud of waging nonviolent struggle to achieve democratic rights and respect the human rights and equal treatment of of the Oromo people. Therefore I have nothing to apologize to this court. If I have to apologize, it would be to my people, for failing to adequately disclose the magnitude of discrimination abuse committed against them on daily bases " 

    After this speech the judge prevented the rest of the prisoners from speaking and hurled them back to jail.

    I
    t is to be remembered that these political prisoners were arrested for helping Amnesty International investigate human rights abuse in Oromia. They were initially accused of treason but later changed to 'terrorism'.

    There are already 25,000-30,000 Oromo political prisoners languishing in various Ethiopian jails