Thursday, August 25, 2016

የነጻነት ጮራ በኢትዮጵያችን በቅርቡ ይፈነጥቃል!!!!












የፈይሳ ሌሊሳ ቤተሰቦች ከሮይተርስ የዜና አውታር ጋር በመኖሪያ ቤቱ ቃለምልልስ አድርገዋል። ወላጅ እናቱ ''መንግስት ቢመለስ 

ምንም አይሆንም ብሏል። ምን ይመስልዎታል?''ተብለው ሲጠየቁ ይህን ምላሽ ሰጥተዋል።





''እኔ አላምንም እዛው ይሁንልኝ። ልጄን እወደዋለሁ ቢመጣልኝ እፈልግ ነበር ነገር ግን ምን አደርጋለሁ። ብዙ ቀናቶች ሳለቅስ አሳልፌያለሁ። አሁን ግን ጥሩ ስሜት ይሰማኛል። እዛው ባለበት እንዲሆንልኝ እፈልጋለሁ። እሱ ብቻ ባለበት ሰላም ይሁንልኝ እንጂ!''

ባለቤቱ በበኩሏ ''በወቅቱ በጣም ፍርሃትና ድንጋጤ ወሮኝ ነበር። ነገርግን አልተገረምኩም ምክንያቱም አውቀዋለሁና። በማኅበራዊ ድረገጾች ላይ የተገደሉ ሰዎችን አካል ሲያይ፣ ሲታሰሩና ሲደበደቡ ሲያይ ውስጡ ይቃጠል ነበር። ባደረገው ያልተገረምኩት የውስጡን ቁጭት ስለማውቀው ነው።''የነጻነት ቁንጮ የጀግኖቹ ጀግናምንም ሳይቸግራው ገንዘብ ወይ መኪና
ወርቅ ፣ናሃስ ፣ብር ሳይል ሳይበግረው ዝና :ሁለት ታዳጊ ሕጻናት ልጆቹን፣ አሮጊት እናቱን፣ ባለቤቱን ትቶ የወገኑን ብሶት በዓለም ዓደባባይ አሰምቷል። የነጻነት ጮራ በኢትዮጵያችን በቅርቡ ይፈነጥቃል። እስከዛው ፈይሳ ሌሊሳ ባለህበት ሰላምህ ይብዛ!!!
..
.



No comments:

Post a Comment