Sunday, September 6, 2015

የህወሀት እስርና እንግልት ያልበገረው ፍቅር





የህወሀት እስርና እንግልት ያልበገረው ፍቅር

ቂሊንጦ የተካሄደው የቀለበት ስነስርዓት





ብዙ ጊዜ ስለተቃራኒ ፆታ ፍቅር መጻፍ ብዙመ አልወድም ወይም አይመቸኝም ይህ ተከታዩን በቂሊንጦ እስር ቤት ከሰሞኑ የተፈፀመው የቀለበት ስነስርዓት ስሠማ ግን የሆነ የተለየ ነገር ሆኖ ስላገኘሁት ትንሽ ፈለግኩኝ፡፡

ጉዳዩ እንዲህ ነው በተደጋጋሚ ከዚህ ቀደም እዚህ ፌስቡክ ላይ እንደገለፅኩት በአንድ ወቅት የአሁኑ የኢትዮጵያ አየር ሐይል አባል የነበረው ወጣት ሻለቃ አክሊሉ መዘነ የገዢውን ፓርቲ ዘረኝነት እና ጭቆና መቋቋም አቃተኝ በማለት የኢትዮጵያ አየር ሀይልን ከድቶ ኤርትራ በመግባት የትጥቅ ትግል እያካሄደ የሚገኘውን አርበኞች ግንቦት 7 ህዝባዊ ሐይልን ይቀላቀላል ወጣቱ የአየር ሐይል አባል ወደአርበኞች ግንቦት 7 መቀላቀሉን የሠሙት የገዢው ፓርቲ ደህንነቶች በቂም በቀል ተነሳስተው የሻለቃ መዘነ ታናሽ ወንድምን ሠይፈ መዘነን ከሚኖርበት ኮተቤ አካባቢ በመያዝ ወደማዕከላዊ በመውሰድ ከፍተኛ ድብደባ የፈፀሙበት ሲሆን በወቅቱም ይህንን ጉዳይ መረጃ አሰባስቤ ይፋ ማውጣቴ ይታወሳል፡፡ እናም ታናሽ ወንድምዬወን ሠይፈ መዘነን ማዕከላዊ ወስደው ከደበደቡት በኋላ ፍርድ ቤት እንኳን ሳይወስዱ በአሁኑ ሠዓት ቂሊንጦ ወስደው አስረውት ይገኛል አስገራሚው ነገር ሠይፈ መዘነ ከጉዳዩ ጋር ምንም አይነት ግኑኝነት የሌለውና ምንም አይነት ፖለቲካዊ ተሳትፎ ያልነበረውና ስለጉዳዩ ምንም ሳያውቅ በግል ስራ ይተዳደር የነበረ ወጣት ነው፡፡

የሠይፈ መዘነን ወደቂሊንጦ እስር ቤት መዛወር የሠማችው ፍቅረኛው ሚዛን ፎቶው ላይ የምንመለከታት እንስት ጓደኞቿን ሰብስባ ቂሊንጦ እስር ቤት ድረስ በመሄድ ለፍቅረኛዋ ለሠይፈ መዘነ የቃልኪዳን ቀለበት አድርጋለታለች፡፡ በዙሪያዋ የሚገኙ ወጣቶች ሰይፈ በቃ ሻለቃው ወንድሙ አክሊሉ ከድቶ ኤርትራ በመግባቱ የህወሀት ሠዎች ለቂም በቀል ሠይፈን ምን አልባት ለበርካታ አመታት ሊያስሩት ይችላሉ የሚል ማስፈራሪያ ቢሠጧትም አሉባልታውንና ማስፈራሪያውን ችላ ብላ ከሠሞኑ ለሠይፈ መዘነ ቀለበት አድርጋለት እንዲህ ብላው ከቂሊንጦ እስር ቤት ለቃ ሄዳለች ""እውነት ማሸነፏ አትቀርም ያኔ አንተ ነፃ ትወጣና የቃልኪዳን ቀለበታችንወደትዳር ቀለበትነት ትለወጣለች እስከዛው ግን እጠብቅሀለው እወድሀለው""

ምስሉ ላይ የምትመለከቷቸው በአሁኑ ሠዓት ቂሊንጦ በእስር ላይ የሚገኘውን ሠይፈ መዘነን እና ፍቅረኛውን ሚዛንን ነው

Ermias Tokuma Alemayehu 

No comments:

Post a Comment