Wednesday, May 22, 2013

ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ በመላው አውሮፓ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ


ማጥራት፣ከቤት ንብረት ማፈናቀል፣ በሙስሊሙም፣ በክርስቲያኑም እየተደረገ ያለውን የሃይማኖት ጣልቃገብነትና ግረፋት፣ እስራት፣ ዛቻና ግድያ አንዲሁም በልማት ስም አየተፈጸመ ያለውን ገደብ ያጣ የመሪት ሽያጭና ስጦታ፣ እየፈጸመ ያለውን ህዝባዊና ሃገራዊ ክህደት ለመቃወምና ለማጋለጥ፣ ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ስልፍ ጁን 19/2013 ከ13:00 ስዓት ጀምሮ በቤልጄም ብራስልስ ሹማን ቁርጥ ቀጠሮ ይዘናል።
እየተፈጸመ ያለውን የዜጎችን መብት ረገጣ፣ የዘር መድሎ እንዲሁም ወያኔያዊ የሃገር ማጥፋት ውል ፍልስፍና በመቃወም! ለሃገረዎ ለወገኖዎ ያለዎትን ክብርና ሃገራዊ ስሜት በዚህ ደማቅ ሰልፍ ላይ በመገኘት ስሜትዎን በግንባር እንዲገልጹ ጥሪያችንን እናቀርባለን!
ከተለያዩ አውሮፓ ሀገራት ለምትመጡ በሃገር ኣቋራጭ አውቶብስ ለመጓጓዝ በድህረ-ገጹ ወይም ማስታወቂያው ላይ ያለውን ስልክ በመደወል ድምጽዎትን በፊት ለፊት ለማሰማት በአካባቢዎ ይደራጁ።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ለበለጠ መረጃ:-
Geneva፡
41223454206, 0041799483736
Belgium፡
0032493499619, 0032493284107, 0032493567554, 0032477327090,
German፡
004917647598748 004915211790603 00492217901605
Sweden፡
004673759578
Italy፡
0039690230273
Norway፡
004745206390

004747163809

Monday, May 20, 2013

ከሙስናው በስተጀርባ

ከኢየሩሳሌም አርአያ
በሕወሐት የተፈጠረው የቀውስ ማእበል አድማሱን እየለጠጠ መሔዱን ተከትሎ «ታማኝ» ሆነው በሙስና ሲያገለግሉ የቆዩትን ጭምር እየበላ እንደሚገኝ የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። በቀዳሚነት የሚያነሱት በጉምሩክ ቁልፍ ስልጣን የነበረውን የሕወሐት አባል ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ሲሆን እንዴትና በማን ወደስልጣን እንደመጣ እንዲሁም ምን-ምን ተግባራት ይፈፅምና ያስፈፅም እንደነበረ ምንጮቹ ሂደቱን እንደሚከተለው ይገልፁታል።
ገ/ዋህድ በ1993ዓ.ም ፓርቲው ለሁለት መሰንጠቁን ተከትሎ ወደ ስልጣን እንዲመጣ ተደረገ። ከጉምሩክ ሃላፊነት በተጨማሪ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተርነት ስልጣን እንዲጨብጥ የተደረገው በአቶ መለስ በተለይ በአዜብ ይሁንታ ጭምር እንደነበረ ምንጮቹ ይጠቁማሉ። ገ/ዋህድ ለዚህ ስልጣን የበቃው ለአቶ መለስ ቡድን በከፈለው መስዋእትነት ሲሆን በክፍፍሉ ማግስት የሙስና ዘመቻ ተከፍቶ እነአባተ ኪሾና ሌሎች እስር ቤት እንዲገቡ ቀጥተኛ ትእዛዝ ከመስጠት አንስቶ ራሱ ክስ አዘጋጅ፣ምስክርና ፈራጅ..በመሆን የላቀ ሚና መጫወቱን ያስታውሳሉ። በዚህ ተግባሩ የበለጠ ታማኝነቱን በማሳየቱ ከአዜብ በሚሰጠው ቀጥታ ትእዛዝ ሙስናውን ማከናወን መቀጠሉን ምንጮቹ አያያዘው ይጠቁማሉ። በ10ሺህ ቶን የሚገመት ቡና ከአዜብ በተቀበለው ትእዛዝ በህገወጥ መንገድ ከአገር ተዘርፎ የተሸጠበትና ጉዳዩም በፓርላማ ተነስቶ በጠ/ሚ/ሩ «የሌቦቹን እጅ እንቆርጣለን» የሚል አስቂኝ ምላሽ መሰጠቱን ያስታውሳሉ። በተጨማሪ በጉምሩክ ለረጅም አመት በመምሪያ ሃላፊነት ሽፋን የተቀመጠውና የቢሮውን የበላይ ሃላፊዎች በጥብቅ ከመቆጣጠር ጀምሮ እያንዳንዱን የሙስና ተግባር ከጀርባ ሆኖ የሚያስፈፅመው የአዜብ የቅርብ ስጋ ዘመድ ፍትሃነገስት ክንደያ እንደሚጠቀስና ግለሰቡ ቀረጥ ያልተከፈለባቸው 500 ሳተላይት ዲሾች እንዲገቡና በአዜብ በበላይነት ይመራ ለነበረው የዘረፋ ቡድን ለሰባት አመታት በየወሩ 20ሚሊዮን ከቴሌ በህገወጥ መንገድ እንዲዘረፍ ያደረገና በኋላም ከነገ/ዋህድ ጋር ሆኖ በርካታ ሙስናዎችን በዋናነት በማስፈፀም እንደሚጠቀስ ያመለክታሉ።
በሌላም በኩል የገ/ዋህድ ባለቤት ኰ/ል ሃይማኖት ስትጠቀስ ከሕወሐት አንጋፋ ሴት ታጋዮች አንዷ ናት፤ ከጡረታ ጋር በተያያዘ ከመከላከያ በመልቀቅ በአዜብ የበላይነት በሚመራው የሴቶች እና ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ቢሮ መስራት ቀጠለች። ለዚህ ቢሮ ከአሜሪካ መንግስት ብቻ በአመት እስከ 240ሚሊዮን ዶላር ይለገሳል። ገንዘቡ ለሚመለከታቸው ወገኖች ሳይሆን የሚውለው የነአዜብ ኪስ ማደለቢያ ሆኖ እንደሚዘረፍ ያመለከቱት ምንጮች ይህም ጉዳይ በፓርላማ ለቀድሞ ጠ/ሚ/ር ተነስቶ « ከእንግዲህ ቁጥጥር እናደርጋለን» የሚል የተድበሰበሰ ምላሽ እንድተሰጠ ያስታውሳሉ። ባልና ሚስቱን በተለያየ ወጥመድ በማስገባት የሙስና ጋሻ-ጃግሬ አድርገው የቆዩት አዜብ እንዲሁም ሌሎቹ ቱባ ባለስልጣናት መጠነ-ሰፊ ዘረፋና ሙስና ጉዳይ ሳይነካ ግልገሎቹን ብቻ (ያውም በአስፈፃሚነት ራሳቸው የመደቧቸውን) ተጠያቂ ማድረግ ተራ ድራማ ነው ሲሉ ምንጮቹ ያጣጥሉታል። በማስረጃነትም፥ 400 ሚሊዮን ብር ለ«ራዲሰን ሆቴል ግንባታ» በሚል ሽፋን በመፍቀድ 150ሚሊዮን ኪሳቸው ከከተቱትና በርካታ ብድሮችን በመፍቀድ (የስጋ ዘመዶቻቸውን ደላላ በማድረግ…) በሙስና የደለቡት አባይ ፀሃዬ ጨምሮ፣ የበታች ሙሰኞች ላይ <ምስክር> ሆነው የቀረቡትና ከአዜብ ጋር በሙስና የሰከሩት አባዱላ ገመዳ፣ የተለያዩ ድርጅቶች ባለቤት ስብሃት ነጋ፣ የቱጃሩን የቢሊዮን ብድር በግል ከመፍቀድ አንስቶ የታዋቂ ባለሃብቶች <ቀኝ እጅ> የሆኑትና ሚስታቸውን ጭምር በሙስና ያሰማሩት በረከት ስምኦን፣ ሶፍያን አህመድ፣ እንዲሁም ቪላዎችን ከ8 እስከ 10 ሚሊዮን ብር ወጪ በማስገንባትና በማከራየት የአገር ሃብት የሚዘርፉ ሁሉም የገዢው ትላልቅ ባለስልጣናት የሙስና ጉዳይ በዋቢነት ይጠቅሳሉ። ባጠቃላይ የስርአቱ ቁንጮዎች የሚያናቁራቸው የገዛ ጥቅምን ከማስጠበቅና አንዱ ጎራ ከሌላው በልጦ በሙስና የሚከብርበትን መንገድ ለማመቻቸት ብሎም ሌላኛውን በመጨፍለቅ ስልጣኑን ከነታማኝ ተከታዮቹ አስጠብቆ የሚቀጥልበትን ብቻ እንደሚያልም የጠቆሙት ምንጮቹ፣ ስርአቱ የአስተዳደር፣የፖለቲካ፣ የፖሊሲ…ወዘተ ልዩነት እንደሌለበት ያሰምሩበታል።

Sunday, May 12, 2013

የኦነግ ወታደሮች አንድ የጸጥታ ሹም ገድለው 7 ፖሊሶችን አቆሰሉ !

የኦነግ ወታደሮች አንድ የጸጥታ ሹም ገድለው 7 ፖሊሶችን አቆሰሉ
ግንቦት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም


በቦረና ዞን ፣ የሚኦ ወረዳ የጸጥታ ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት አቶ ጁኬ የአካባቢውን ፖሊሶች በማሰልፍ የኦነግን ታጣቂዎች ለማደን ሚያዚያ 29፣ 2005 ዓም ቢንቀሳቀሱም የኦነግ ወታደሮች ጨሶ እና ሜጢ በሚባል ቦታ ላይ አድፍጠው በመጠበቅ በወሰዱት እርምጃ ፣ የጸጥታ ሹሙን አቶ ጁኬን ገድለው፣ 7 ፖሊሶች ደግሞ አቁስለዋል። 6ቱ ፖሊሶች በያቤሎ ሆስፒታል ተኝተው በመታከም ላይ ሲሆኑ አንዱ ፖሊስ ደግሞ በጽኑ በመቁሰሉ ወደ አዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ተወስዷል ። የክልሉ የጸጥታ ዘርፍ ሹም የቀብር ስነስርአትም ግንቦት 1 ፣ 2005 ዓም በኢዲሎላ ከተማ መፈጸሙን የአካባቢው ወኪላችን ገልጿል።






ኢሳት ዜና


Thursday, May 9, 2013

150,000 Oromo people Displaced From Their Homes In Harerghe,Oromiya

150,000 Oromo people Displaced From Their Homes In Harerghe,Oromiya After Special Force Sent In 11 Towns By TPLF Ruling Class To Rob & Kill Ethnic Oromo People .Eyewithness said the Special Force have tied to Ethiopia Govt & TPLF Ruling Class.This news aired on 5.3.2013 On ESAT Radio.bilisummaatv@gmail.com 2013 BilisummaaTV Oromia






ሰማያዊ ፓርቲ የአፍሪካ ኅብረት 50ኛ ዓመት በዓል ሲከበር ሰላማዊ ሠልፍ ለመጥራት መወሰኑን አስታወቀ


በኢትዮጵያ የሚፈጸሙ የተለያዩ የሰብዓዊ፣ ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶችና ሕገወጥ ድርጊቶች እንዲቆሙ ለመንግሥት በተለያዩ 
ጊዜያት ጥያቄዎችን ቢያቀርብም፣ ከመንግሥት በኩል ምንም ምላሽ ማግኘት ባለመቻሉ የአፍሪካ ኅብረት 50ኛ ዓመት በዓል በሚከበርበት ወቅት፣ ጥቁር ልብስ በመልበስ ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ መወሰኑን ሰማያዊ ፓርቲ አስታወቀ፡፡ 





ማክሰኞ ማለዳ በጽሕፈት ቤቱ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጠው ሰማያዊ ፓርቲ፣ ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም. በሚከበረው የአፍሪካ ኅብረት 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓልና በዓሉ ከሚከበርበት ሁለት ቀናት ቀደም ብሎ ከግንቦት 15 ቀን ጀምሮ ሕዝቡ ጥቁር ልብስ እንዲለብስ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡ “የአሜሪካ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ሁሉም የአፍሪካ መሪዎች፣ የሌሎች አገሮች መንግሥታትና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች በሚገኙበትና በሚሰበሰቡበት የአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ ፊት ለፊት ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም. ሰላማዊ ሠልፍ በማድረግ ድምፃችንን እናሰማለን፤” ያሉት የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበርና የምርጫ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ስለሺ በይሳ ናቸው፡፡ 
ኃላፊው እንዳብራሩት፣ ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ሥርዓት መስፈን የሚታገሉ ጋዜጠኞች፣ የፓለቲካ ፓርቲዎችና አባላትን በአሸባሪነት ስም ማሰቃየትን ፓርቲው ይቃወማል፡፡ መንግሥት የታሰሩትን እንዲፈታም ጠይቋል፡፡ ዜጎች ሕገ መንግሥታዊ መብቶቻቸው ተጥሷል፡፡ ከኖሩበት ቦታ በታጠቁ ኃይሎች እንዲፈናቀሉ ማድረግ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው፡፡ በመሆኑም ድርጊቱን የፈጸሙ ለፍርድ መቅረብ እንዳለባቸው ፓርቲው ሌላ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ 
መንግሥት በሃይማኖታችን ጣልቃ አይግባ ብለው የጠየቁ የእስልምና ዕምነት ተከታዮች ታስረዋል፡፡ በአሸባሪነት ወንጀልም ተከሰዋል፡፡ በእስር እንዲማቅቁና ሰብዓዊ መብታቸው እንዲጣስ መደረጉ እንዲቆም ፓርቲው መጠየቁን፣ መንግሥት የኑሮ ውድነትን፣ ሥራ አጥነትንና በሙስና የተዘፈቁ ሹማምንትን ፖሊሲ በማውጣት እንዲቆጣጠር ቢጠየቅም፣ ጥያቄዎቹን ከማንቋሸሽ፣ ከማጣጣልና ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ከማለፍ ውጪ ምንም ምላሽ አለመስጠቱን ገልጸዋል፡፡ 
በመሆኑም ሰማያዊ ፓርቲ የመግለጫ ፓርቲ ብቻ ሳይሆን፣ ሰላማዊ ትግል የሚፈቅደውንና በሕገ መንግሥቱ የተፈቀደውን ለማድረግ ጠንክሮ እየሠራ መሆኑን አቶ ስለሺ ተናግረዋል፡፡ 
ፓርቲው በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ መሆኑን፣ የሚቻለውን ሁሉ እያደረገና በሕዝብ ዘንድም ተቀባይነቱ እየጨመረ መምጣቱን የሚናገሩት ምክትል ሊቀመንበሩ፣ ከነባር ፓርቲዎች ባልተናነሰ እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ 
ፓርቲው በሐዋሳ፣ በምሥራቅ ጐጃም፣በ ሸካ፣ በጐንደርና በድሬዳዋ የዞን አስተባባሪዎች እንዳሉት የገለጹት አቶ ስለሺ፣ ከገንዘብ ጀምሮ ብዙ ችግሮች ቢኖርባቸውም፣ በአባሎቻቸው ላይ እየደረሰ ያለውን ተፅዕኖ በመቋቋም ጠንክረው እየሠሩ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ 
ከፍተኛ አመራሩም ሆነ የምክር ቤቱ አባላት እንደሚተማመኑና ከልባቸው እየታገሉ መሆኑን የገለጹት አቶ ስለሺ፣ አንዳንዶቹ በሌላ ፓርቲ ውስጥ የነበሩና አለመተማመን ያመጣው ጣጣ ሰለባ የነበሩ ስለሆኑ በደንብ እንደሚተዋወቁ በመግለጽ፣ እርስ በርሳቸው አንዱ አንዱን በመሰለል ለገዢው ፓርቲ መረጃ ያቀብላል ለሚለው አሉታ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ 
በሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ ሆነው ለገዢው ፓርቲ መረጃ የሚያቀብሉ እንዳሉና አልፎ አልፎም ተለጣፊ ፓርቲ እንደሆነ ስለሚነገረው ጉዳይ ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ስለሺ፣ “እዚህ አገር ተሰባስበህ ስትሠራ ስም ይሰጥሃል፡፡ ከቅንጅትና ከአንድነት ጋር ቢያያይዙን እውነት ነው፡፡ ከኢሕአዴግ ጋር ግን እንኳ በፖለቲካ ደረጃ የሥራም ግንኙነት የነበረው አባል የለንም፤” ብለዋል፡፡ 
የፓርቲ አባላት የፖለቲካ እንቅስቃሴ ገብቷቸው ሳይሆን የጥገኝነት መጠየቂያ ሰነድ ለማግኘት አባል እንደሚሆኑ፣ ለዚህም ማረጋገጫ በቅርቡ በአመራር ደረጃ የነበረ አባል መሰደዱን በሚመለከት ማብራሪያ የሰጡት አቶ ስለሺ፣ ‹‹አይኖርም ማለት አይቻልም›› ካሉ በኋላ፣ በቅርቡ ተሰዷል ስለተባለው አባላቸው ደግሞ ‹‹አባሉ ጌታቸው አርዓያ ይባላል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ መሥራችና ስሙንም የሰየመው እሱ ነበር፡፡ የሥራ አስፈጻሚና የምክር ቤት አባልም ነበር፡፡ ከሰባት ወራት በፊት ግን ማመልከቻ በማቅረብ ከአመራርነት ወርዶ በተራ አባልነት ቀጥሎ ነበር፤” ብለው፣ የፓርቲው አባል ከመሆኑ በተጨማሪ ፍትሕ ጋዜጣ ላይ ይሠራ ስለነበር ደኅንነቶች እየተከታተሉት እንደተቸገረ እንደነገራቸውና በኋላም ተሰዷል መባሉን እንደሰሙ ተናግረዋል፡፡ 

Monday, May 6, 2013

የኢትዮጵያው ፀረ-ሽብር ሕግ የፕሬስ ነፃነትን አውድሟል

የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት ሣይንስና ባህል ድርጅት፣ እንዲሁም ለነፃ ፕሬስ መከበር የቆሙ ሌሎች ድርጅቶች የዛሬውን ዓለምአቀፍ የፕሬስ ነፃነት ቀን ምክንያት በማድረግ የዓለም ጋዜጠኞች ደህንነት እንዲረጋገጥ ጥሪ አድርገዋል።
ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት - ሂዩማን ራይትስ ዋች በበኩሉ የዛሬውን የዓለም የነፃ ፕሬስ ቀን ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያን ፀረ-ሽብር ህግ በመተቸት መግለጫ አውጥቷል።

ኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ በአቶ አንዱዓለም አራጌና በሌሎች ተከሣሾች ላይ ያፀናውን ፍርድ በመቃወም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት መግለጫ አውጥቷል፡፡


“የኢትዮጵያው ፀረ-ሽብር ሕግ የፕሬስ ነፃነትን አውድሟል” ይላል ለሰብዓዊ መብቶች መከበር የሚሟገተው መንግሥታዊ ያልሆነ ነፃ ድርጅት ሂዩማን ራይትስ ዋች ያወጣው መግለጫ ርዕስ፡፡

በናይሮቢ-ኬንያ የድርጅቱ ጥናት አቅራቢ ለቲሺያ ቤደር መግለጫውን ሲያብራሩ “ዓለም የፕሬስ ነፃነትን አክብሮ በሚውልበት በዛሬው ቀን ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ጋዜጠኞች ታስረው እንደሚገኙና አንዳንዶቹም በአገሪቱ ፀረ-ሽብር ሕግ የተፈረደባቸው እንደሆኑ ይህ ሕግም ከረቂቁ ጀምሮ ፀድቆ ሕግ እስከሆነበት ጊዜ ድረስ አሳሳቢ መሆኑንና የመናገር መብትን የሚያፍን መሆኑን ነው የገለፅነው።” ብለዋል፡፡

ሂዩማን ራይትስ ዋች እአአ ከ2011 ጀምሮ አሥራ አንድ ጋዜጠኞች /ስድስቱ በሌሉበት/ አፋኝ ባለው ፀረ-ሽብር ህግ ተከስሰው እንደተፈረደባቸው ይገልፃል።


በአሁኑ ወቅት በፀረ ሽብር ሕጉ የተከሰሱና ተፈርዶባቸው እሥር ቤት የሚገኙ ጋዜጠኞች በአጠቃላይ አምስት መሆናቸውን፤ እነርሱም እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ እና ውብሸት ታየ፣ እንዲሁም በፀረ-ሽብር ሕጉ ተከስሰው ፍርድ የሚጠባበቁ ሁለት ደግሞ ዩሱፍ ጌታቸውና ሰሎሞን ከበደ መሆናቸውን ለቲሺያ ቤደር ጠቅሰው የኢትዮጵያ መንግሥት የታሠሩትን በፍጥነት ከእሥር እንዲፈታ ጠይቀዋል።

“እአአ በ2009 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፀረ-ሽብር ሕግ ከፀደቀ ወዲህ ነፃ መገናኛ ብዙኃንን አሳብቦ ለማሳደድ በያዘው ሕግ የኢትዮጵያ ነፃ ጋዜጦች ተንኮታኩተዋል” ይላል የሂዩማን ራይትስ ዋች መግለጫ፡፡

መንግሥት ሆን ብሎ ጋዜጠኞች እንዳያሣትሙ እንደሚያደርግ፣ በኢንተርኔት የሚተቹትን ጽሁፎች እንደሚጋርድ፤ የማስተዋል አሣታሚ ባለቤት የሆነውን ማስተዋል ብርሃኑን እና የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረውን ተመስገን ደሣለኝን በዚሁ ፀረ-ሽብር ሕግ ከስሦ እንደሚያጉላላ ገልጿል።

የኢትዮጵያ መንግሥት እንደ ሂዩማን ራይትስ ዋች እና የጋዜጠኞች ደህንነት ተሟጋቹ ኮሚቴ - ሲፒጄ ያሉ ድርጅቶች የሚሠነዝሩበትን የመብት ጥሰት ነቀፋ አይቀበልም።

ባለሥልጣናቱ “ኔኦ-ሊብራልና የምዕራቡን የነፃነት ፍልስፍና ለማስፋፋት የሚሠሩ” ሲሉ ይተቿቸዋል፡፡ የአሁኑ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማሪያም ደሣለኝ በአንድ ወቅት ስለሰብዓዊ መብቶችና የመናገር ነፃነት በአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጋዜጠኛ ተጠይቀው “እኛ የምንከተለው የቻይናን ልማታዊ ዴሞክራሲ እንጂ የምዕራቡን ፍልስፍና አይደለም” ማለታቸውን ለሂዩማን ራይትስዋ አጥኚ አንስቼ ነበር።

“ጥሪአችን ስለ ርዕዮተ-ዓለም አይደለም በዓለም አቀፍ ደረጃ ሰለተደነገጉት የሰው ልጆች መብቶች እንጂ” ይላሉ ለቲሺያ ቤደር …
የሂዩማን ራይትስ ዋች የአፍሪካ ፕሮግራም ዳይሬክተርና የኢትዮጵያና የኤርትራ ጉዳዮች ኃላፊ ሌስሊ ሌፍኮ በበኩላቸው እአአ በ2007 ዓ.ም ኢትዮጵያ እሥር ቤት ውስጥ የሚገኙ ሁለት የኤርትራ ጋዜጠኞች ሳላህ ኢዲሪስ ጃማ እና ተስፋልደት ኪዳኔ ተስፋዝጊ ደህንነት ድርጅታቸውን እንደሚያሳስብ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት የእነዚህን ሁለት ጋዜጠኞች በጠበቃ የመወከል መብታቸውን እንዲያከብር፣ እንደ ዓለምአቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ባሉ ነፃ አካላት እንዲጎበኙ፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ በሕይወት መኖራቸውን እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል።

Thursday, May 2, 2013

Breaking News: TPLF sentenced Eskinder Nega and Andualem Arage








Ethiopia confirms jail for blogger, opposition figure
* Ethiopia has one of the most restricted media in the world and the highest number of journalists living in exile
An Ethiopian Kangaroo court on Thursday dismissed the appeal of blogger Eskinder Nega and opposition leader Andualem Arage who were jailed last year for terror-related offences.

"The sentencing is still correct so there is no reduction," said Supreme Court judge Dagne Melaku, confirming Eskinder's jail term of 18 years and Andualem's life sentence.

One of the charges -- serving as a leader of a terrorist organisation -- was dropped, but had no affect on sentencing. After the ruling, Eskinder made an emotional appeal to the court which was crowded with family, friends and diplomats. "The truth will set us free," he said. "We want the Ethiopian public to know that the truth will reveal itself, it's only a matter of time."

Both men are accused of links to the outlawed opposition group Ginbot 7. "The walls of justice will be demolished," Andualem told . Four other men also jailed for terror-related charges had their appeal quashed.

One other defendant, however, Kinfe Michael, had his sentence reduced from 25 years to 16 years. Rights groups have called Ethiopia's anti-terrorism legislation vague and accuse the government of using the law to stifle peaceful dissent.

"I am very sad, I am very angry, I cannot talk rationally," Eskinder's wife Serkalem Fasil told   after the decision.

Defence lawyer Abebe Guta said that justice had not been served, and that if his clients agreed, they would appeal to court of cassation, Ethiopia's highest court. Ethiopia has one of the most restricted media in the world and the highest number of journalists living in exile, according to US-based press watchdog, the Committee to Protect Journalists.

Last year Eskinder was awarded the prestigious PEN America's "Freedom to Write" annual prize. Rights groups including Amnesty International and Human Rights Watch condemned the initial conviction of the Eskinder in July 2012.