Saturday, March 25, 2017

አንድ እስረኛ ተመርምሮ ሲመለስ መጀመሪያ የሚቀርብለት ጥያቄ 'ተሰቅለህ ነበር ወይም አልተሰቀልክም? የሚል ነው"ከእስር የተለቀቁት አቶ ሐብታሙ አያሌው።




Habtamu Ayalew on VOA : says of something horrible at TPLF's torture centers which he is not willing to disclose on moral and religious grounds unEthiopian , . . You can easily guess that . . . A dehumanizing , demeaning Sexual abuse by security agents is widespread ,. . . Sad ! !
 In deed it's unEthipoian..... sodomy is the most inhuman barbaric act. 
But for me what I found even more shocking and hurt breaking is the fact that we the society seemed to no longer be outraged enough to rise up to say enough is enough and put a stop to it in order regain our dignity and humanity back....we keep saying 'oh that's sad' and that's it.
The former spokesman for the opposition party accused of terrorism offenses in prison are serious blow as a result of the investigation during the two years of suffering now say has included health crisis.

Brutalities perpetrated in prisons, degrading various types of diagnostic inidemiderigumi the same health problems, including his predecessor

Monday, October 24, 2016

የሕወሃት ወታደራዊ አገዛዝ !



የሕወሃት ወታደራዊ አገዛዝ የተጨማለቀ የሕግ ስርዓት :

የሕወሃት አገዛዝ አንዱ ባህሪዉና መለያው ዜጎችን ማሰቃየት ነው። ማሰር እንጂ መፍታት፣ መጣል እንጂ ማንሳት፣ መግደል እንጂ ማዳን፣ ማዋረድ እንጂ ማክበር፣ መስበር እንጂ መጠግን ፣ መከፋፈል እንጅ አንድ ማድርግ አያወቁበትም። እንደ እንስሳት ጉዳዮችና ልዩነቶችን በሃይልና በጡንቻ መፍታት እንጅ እንደ ሰለጠነ ሰው በሰለጠነ መንገድ መፍታት አለመፈለግ ብቻ ሳይሆን ብቃቱ የለዉም።

ለስሙ ፍርድ ቤት፣ ዳኛ፣ ሕግ ፣ ሕገ መንግስት እያሉ ህወሃቶች ጠዋትና ማታ ያሰለቹናል። ሆኖም ግን በኢትዮጵያ ታሪክ እንደነርሱ ሕግን መቀለጃና ማሾፊያ ያደረገ አገዛዝ የለም :የወያኔ የጅምላ እስራትና ግድያውን ቢያስፋፋም ሕዝባዊ ተቃውሞው እንደቀጠለ ነው

አሀኡነማ ሰው መግደለ ማሰረ መሰ ቃ የት ሕጋአው አደረጉተ ዱ ርአ ውነሰ ሀገአረዋት
ግን ግ ዜ ው ደረሰዋል: ወያኔ ዝቅ ብሎ የሚለምንበት !!

 

Tuesday, October 11, 2016

በህዝብ ላይ ጦርነት አውጆ ያሸነፈ የለም





የስርዓቱ መውደቅ ጫፍ ላይ ደርሷል። ከዚህ በኋላ የትኛውም ጥገና አያተርፈውም። በገንዘብ የሚፈወስ አይደለም። ደምወዝ በመጨመር የሚተርፍ አይደለም። ዘግይቷል። ረፍዷል። ህወሀት መጠየቅ ያለበት መውጪያ መንገድ ብቻ ነው።




የወያኔ የጊዜአዊ አዋጅ ድንፋታና የሆዳም የካዲሬዎቹ ጫጫታ ሕዝባዊ ትግሉን አይበገረውም። እንዲያውም አስቆጥቶና እልክ አሰግበቶ የበለጠ ሕዝቡን ወደ ትግል ያስገባዋል እንጂ ! ስለሆነም ይህንን ጉግ ማንጉግ፡ ሞራልና ሕሊና የሌለው፡ ከፀረ ሀይማኖትና ከፀረ እግዚአብሔር አልፎ ፡ ፀረ-የሰው ልጅ የሆነውን የመህይም ጥርቃሞ ቲፒ ኤል ኤፍ TPLF (ወያኔ/ኢሕአደግ) የሚባለውን የማፊያ ቡድን ከመላ ኢትዮጵያ ለማጥፋት... በዘር፡ በሀይማኖት፡ በፖሌቲካና በኢኮኖሚ ሳንለያይ አንድ ሁነን ታግለን የድሉን ቀን እናቅርበው እላለሁ። የወቀቱ መፈክር "እየተደራጁ መታገል፡ እየታገሉ ነፃነት" መሆን አለበት !

ከዚህ በኋላእኛ ስንሰርቅና ስንከብር እናንተ ዝም ብ ለችሁ ተመለከቱ በቃ ዘ ር ፍ በቃ !!! የትግራይ ነፃ አውጪው የወያኔ ከፍተኛ ባለስልጣናት 11% አገሪቱን አሳድገናል ብለው ነገር ግን ሃቁ ከ20 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ከኃይለ ሥላሴም፣ ከደርግም እጂግ በከፋ ቁጥር ተርቦ እነሱን ለማትረፍ ዓለም በሚረባረብበት ጊዜ እነሱ ከኢትዮጵያ ህዝብ ሌት ከቀን በመዝረፍ አገር ውስጥ ከገነቡት ትላልቅ ህንፃ፣ ቪላና የተለያዩ ድርጅቶች ውጪ በተለያዩ ዓለማት የውጪ ባንኮች ያስቀመጡት ገንዘብ ብዛት በአሜሪካን ዶላር $ 22,572,000,000 (ሀያ ሁለት ቢሊዮን አምስት መቶ ሰባ ሁለት ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር

Thursday, August 25, 2016

የነጻነት ጮራ በኢትዮጵያችን በቅርቡ ይፈነጥቃል!!!!












የፈይሳ ሌሊሳ ቤተሰቦች ከሮይተርስ የዜና አውታር ጋር በመኖሪያ ቤቱ ቃለምልልስ አድርገዋል። ወላጅ እናቱ ''መንግስት ቢመለስ 

ምንም አይሆንም ብሏል። ምን ይመስልዎታል?''ተብለው ሲጠየቁ ይህን ምላሽ ሰጥተዋል።





''እኔ አላምንም እዛው ይሁንልኝ። ልጄን እወደዋለሁ ቢመጣልኝ እፈልግ ነበር ነገር ግን ምን አደርጋለሁ። ብዙ ቀናቶች ሳለቅስ አሳልፌያለሁ። አሁን ግን ጥሩ ስሜት ይሰማኛል። እዛው ባለበት እንዲሆንልኝ እፈልጋለሁ። እሱ ብቻ ባለበት ሰላም ይሁንልኝ እንጂ!''

ባለቤቱ በበኩሏ ''በወቅቱ በጣም ፍርሃትና ድንጋጤ ወሮኝ ነበር። ነገርግን አልተገረምኩም ምክንያቱም አውቀዋለሁና። በማኅበራዊ ድረገጾች ላይ የተገደሉ ሰዎችን አካል ሲያይ፣ ሲታሰሩና ሲደበደቡ ሲያይ ውስጡ ይቃጠል ነበር። ባደረገው ያልተገረምኩት የውስጡን ቁጭት ስለማውቀው ነው።''የነጻነት ቁንጮ የጀግኖቹ ጀግናምንም ሳይቸግራው ገንዘብ ወይ መኪና
ወርቅ ፣ናሃስ ፣ብር ሳይል ሳይበግረው ዝና :ሁለት ታዳጊ ሕጻናት ልጆቹን፣ አሮጊት እናቱን፣ ባለቤቱን ትቶ የወገኑን ብሶት በዓለም ዓደባባይ አሰምቷል። የነጻነት ጮራ በኢትዮጵያችን በቅርቡ ይፈነጥቃል። እስከዛው ፈይሳ ሌሊሳ ባለህበት ሰላምህ ይብዛ!!!
..
.



Tuesday, August 16, 2016

ኃላፊነት የማይሰማው መንግሥት ነው!!!



አንጋፋው የተቃውሞ ፖለቲከኛ ዶክተር መረራ ጉዲና ሀገራቸው ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት ሁኔታ ወደ የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ለመግባት መንታ መንገድ ላይ መቆሟን ተናገሩ፡፡

"ብዙ ህዝብ ባለፉት 25 አመታት አገዛዙ በፈጸመበት ጭቆና መማረሩን የተናገሩት ዶክተር መረራ አሁን ላይ በየቦታው ሰዎች ለተቃውሞ በየአደባባዩ መውጣታቸውንና በዚህም የተነሳ ከፍተኛ የሰብአዊ ቀውስ እየደረሰ መሆኑን ጠቁመው ይህ ሁኔታ ባለበት ከቀጠለ ደግሞ የእርስ በእርስ ጦርነት ሊከሰት ይችላል የሚል ስጋታቸውን ገልጸዋል"

፡፡-+የተቃወመውን ወይም በቀጥታ ድጋፍ ያልሰጠውን ሁሉ ፀረ ሰላም፣ ፀረ ልማት፣ ፀረ ዴሞክራሲ፣ ደርግ ናፋቂ፣ የደርግ ርዝራዥ፣ የሻዓቢያ ተላላኪ፣ አሸባሪዎች፣ ኪራይ ሰብሳቢዎች ወዘተ የዕለት ከዕለት ማጣጣያ ከሆኑ ቆይቷል። ህገ መንግስቱ አክብረው፣ በሰላማዊ ትግል የሚታገሉ ድርጅቶችን የአሸባሪነት ስም በመለጠፍ ትግሉ አቅጣጫውን እንዲስት በመገፋፋት፤ ህብረተሰቡ ነፃ ሆኖ እንዳይኖር እንዳይናገር፣ እንዳይፅፍ፣ እንዳይቃወም፣ እንዳይደራጅ በስጋትና ጭንቀት በአገሩ ነፃ ዜጋ ሆኖ እንዳይኖር እየተደረገ ነው፡፡ ሀገሪቱ እኛ ከሌለን ያልቅላታል የሚሉ በስልጣን ላይ ያለው አካል ብቻ ነው ያለነሱ መሪ ያለነሱ አልሚ ያልነበረ ለወደፊቱም የማይኖር ማይመስላቸው ስልጣኑን አኝ አርገው አለቅ ያሉት ;;

ህዋሃትም በሰሞኑ ዘገባው ባለፉት ወራት ሲታዩ የነበሩትን ህዝባዊ ተቃውሞ እንደ ተራ ጩኸት እያጣጣለው ልክ እንደ ደርግ "በጩኸት የፈረሰች ከተማ እያሪኮ ብቻ ነች" የሚል አይነት እድምታ ያላቸው መግለጫዎች እያሰሙ ነው። ዛሬ እንዲህ አይነት መግለጫ ፍሬ ቢስ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ ቱኒዚያ፣ ግብፅ፣ ሊቢያ… በጩኸት ከፈረሱ በኋላ፡፡ በግብፅ አብዮት ወቅት አንድ የትጥቅ ትግል የሚያካሄድ ተቃዋሚ ድርጅትን ይመሩ የነበሩ ከማል ሀቢብ የተባሉ ሆስኒ ሙባረክ በወደቁ ማግስት Tahrir Square (በነፃነት አደባባይ) በአፕሪል18 ቀን 2011ዓ.ም ለታተመው Time መጽሔት "እኛ ለ40 አመት በጠመንጃ መገልበጥ ያልቻልነውን ህዝቡ ያለአንዳች የጦር መሳሪያ በ18 ቀን ውስጥ እውን አደረገው" ብለው በመገረም ተናግረዋል።

ሰላማዊ ህዝባዊ የአደባባይ ተቃውሞና ጩኸት መንግስትን ባያሰጋው ኖሮ ለምን ሰው አደባባይ እንዳይወጣ ይከለክላል?

እሪሪሪ ብሎ መጮህ ነፃነት ያስገኛል። ስለዚህ እንጩህ !!

Friday, February 19, 2016

አገሪቷ ትልቅ ችግር ላይ ናት !





ኦሮሚያ ክልል የጦርነት ቀጠና ሆናለች። እነ ጀነራል ሶሞራ በጭካኔና በግፍ ሕዝቡን በጥይት እያረገፊት ነው"" ባለፉት 3፣ 4 ቀናት ብቻ ቢያንስ ወደ መቶ የሚጠጉ ወገኖቻችን ተገድለዋል። "ቢያንስ" የሚለው ላይ አስመርበታለሁ። ለምን እጅግ በጣም ብዙ የቆሰሉ አሉ። የቆሰለ ሁሉም ይደናል ማለት አይደለም። ሃኩም ሄዶ መሞትም አለ።፡

በጣም ያሳዝናል.....በጣም ልብን ያደማል። አለም በሰለጠነችበት በዚህ 21ኛው አለም፣ እንደ ረሃብ፣ ድርቅ፣ ድህነት የመሳሰሉ የሁላችንም ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ችግሮች እያሉን፣ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሚባለው፣ በአጋዚዎች እጆች ላለፉት 25 አመታት እንደነበረው አሁን ዜጎች እየተገደሉ መሆናቸው በጣም ይሳዝናል።

በሜዳ ላይ ያለውን ሁኔታ እንደሚያሳየው ተቃዉሞው በጣም ተባብሷል። ከአዲስ አበባ ወደ ሃረር ፣ ከአዲስ አበባ ወደ ነቀምቴ ፣ ከነቀምቴ ወደ ጂማ፣ ከሻሸመኔ ወደ ባሌ ....የሚወስዱ መንገዶች ተዘግተዋል። በብዙ ቦታዎች የኦሮሚያ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በቀጥታ ከፌዴራሎች ጋርም ግብግብ የፈጠሩበት ሁኔታ ነው ያለው። ሰላማዊ የሆነው እንቅስቃሴ፣ ወያኔዎች የኃይል እርምጃ በወሰዱ ቁጥር ወደ አመጽ መሸጋገሩ አይቀርም። እየተሸጋገረም ነው።


አገሪቷ ትልቅ ችግር ላይ ናት !

‎OromoProtest‬

Saturday, December 19, 2015

የመንግሥት ኃይሎች ኦሮሚያ ውስጥ እየወሰዱ ያሉት እርምጃ “እጅግ አስከፊ” ወይም በእንግሊዝኛው ቀጥተኛ አባባል “ብሩታል

"ጥቂቶች በብርሀን ፍጥነት ተዝቆ ወደማያልቅ ሀብት የተመነጠቁበት መንኮራኩር፣ መሬት "

ከ5 ዓመታት በፊት እኚህ ክቡር ሰው ሲናገሩ መስሚያ ጆሮ ቢኖራችሁ ዛሬ መያዣ መጨበጫ ባልጠፋችሁ። በነገራችን ላይ ይህ የአቶ በቀለ ገርባ ንግግር እና የአቶ አንዷለም አራጌ ንግግር ምንጊዜም ልቤን የሚያነሳሳኝ፣ በሀገሬ ተስፋ ከሚሰጡኝ መሳጭ ንግግሮች ዋነኞቹ ናቸው

ሀገር መምራት ቀላል እንዳልሆነ እናውቃለን ነገር ግን ከዓመት ዓመት የሕዝቡን ብሶት እያዳመጠ እየተሻለው፣ ልምድ እየቀሰመ ሀገሪቱን ሕዝቡን ወደፊት ማራመድ ሲገባው ከዕለት ወደ ዕለት ወደኋላ እየተመለሰ፣ የኋሊት እየሄደ ሀገሪቱን መምራት ወደማይችልበት ደረጃ ደርሷል::

የኤፌድሪ ሕግ መንግስት እንደሚናገረው ፣ የገዢው ሥርዓት የፖሊሲ ሰነድ እንደሚገልጸው መሬት የመንግስት እና የሕዝብ ነው ይላል:: ነገርግን መሬት የሕዝብ ነው፣ የመንግስት ነው፣ የሁለቱም ነው? መሬት የማንም አይደለም:: መሬት የገዢ ባለስልጣኖች የግል ንብረት ነው::

እንደፈለገ የሚሸጡት፣ የሚለውጡት፣ ጓደኛ የሚያፈሩበት፣ በዘመድ አዝማድ የሚያከፋፍሉት፣ ለወገን እያሉ ለነሱ ፓርቲ አባላት መመልመያ የሚጠቀሙበት ማማለያ ነው መሬት::

*መሬት የተማረውን ሳይቀር፡ ምሁሩን ሳይቀር ማሳወርያ ሆኗል። ዛሬ ምሁሩን አንዳንድ ቦታ በአበዛኛው በምንመለከትበት ጊዜ ስለፍትሕ፣ ስለመብት፣ ስለ እኩልነት የማያወራበት ጊዜ ደርሷል።ምክንያቱ ይኼ ማሳወርያ ነው ዛሬ በየከተማው እና በአዲስ አበባ ዙርያና ሌሎች ከተሞች አካባቢ በብዛት መሬት እየተሰጣችው አፋቸው ተሸብቧል።ስለዚህ መሬት አፍ መሸበቢያ ነው።

* መሬት ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል ውጭ የሚኖረውን ኢትዮጵያዊ መሳቢያ ማግኔት ሆኗል። ዳያስፖራ እየተባለ በአንድ ወቅት ግር... ብለው መጥተው፣ እዚህ ወገኖቻችን ሜዳ ላይ ወድቀው አንዲት ስንዝር መሬት የሌላቸው ወገኖች እያሉ በውጭ ቢያንስ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች መጥተው መሬት ተቀራምተው ሽጠውት ሄደዋል። ስለዚህ ማግኔት ነው የምንለው ለዚህ ነው።
*መሬት ዛሬ ጥቂቶች በብርሀን ፍጥነት ተዝቆ ወደማያልቅ ሀብት የተመነጠቁበት መንኮራኩር ነው።
ብንመለከት፣ እነድውም አንዳንዶቹን ሀብታሞች ብንጠይቃቸው... በሕዝቡ ዘንድ "ታሪኬ በአጭሩ" እየተባሉ የሚጠሩ አሉ። "እንዴት ነው፣ ይህ ሀብት ከየት መጣ እንዴት አገኛችሁ?" ተብለው ቢጠየቁ "እንደዚህ አድርጌ፣ እንደዚህ ለፍቼ አመጣሁ..." ማለት እንኳ የማይችሉ፣ገንዘቡን እንዴት እንዳፈሩት የማያውቁ...ስለዚህ ዛሬ መሬት እንደዚህ ነው:: መሬት የምንም አይደለም
መሬት ወሳኝ ሀብት መሆኑን እናውቃለን::
እኛ ኢትዮጵያዊያን ከዚህ ሀብት ጋራ ባለን ግንኙነት ምክንያት የዜገነት ደረጃችን በ4 ቦታ የተከፈለ ይመስለኛል:-->

1.መሬቱን የሚሸጡ አሉ አንደኛ ደረጃ ዜጎች
2.መሬቱን ከነሱ የሚቀበሉ አሉ፣ ሁለተኛ ደረጃ ዜጎች

3.እነሱ ሲቀባበሉ ቁጭ ብሎ ትዕይንቱን የሚመለከተ ዜጋ ደግሞ አለ ፤ ሦስተኛ ደረጃ- የበይ ተመልካች
4.መሬቱን ተነጥቆ፣ እትብቱ ከተቀበረበት፣ ተወልዶ ካደገበት መሬቱ ሥፍራ እየተባረረ መሬቱ ለሌላ የሚሰጥ የዚህ ድርጊት ሰለባ የሆነ አርሶ አደር ደግሞ አለ::

እኛ ምንታገለው ለዚህ ነው!!!

*****ደግማችሁ ደጋግማችሁ አድምጡት፣ የተቃውሞው መሠረታዊ ጥያቄዎች ያልገባችሁ ፍንትው ይልላችኋል። ይህ የጭቁን ኢትዮጵያዊያን ጥያቄ ነው!
የመንግሥት ኃይሎች ኦሮሚያ ውስጥ እየወሰዱ ያሉት እርምጃ “እጅግ አስከፊ” ወይም በእንግሊዝኛው ቀጥተኛ አባባል “ብሩታል” ናቸው ሲል ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አውግዟል

Sunday, October 18, 2015

BREAKING NEWS

BREAKING NEWS

**********************

The public meeting convened by Oromo Federalist Congress (OFC) in Finfinne Sunday, October 18, to discuss the so-called Addis Ababa and Oromia Special Zone Integrated Development Master Plan has ended adopting a 9-point resolution expected to be announced by OFC in an official press release. Sources say the meeting concluded that the Master Plan is a land grab policy disguised as a development plan and called on Ethiopian authorities to halt it, and on the public to continue rejecting it.

Saturday, October 17, 2015

365 DAYS IN PRISON

ፍትሕና ልዕልና ጋዜጦች፣ እንዲሁም የፋክትና የአዲስ ታይምስ መፅሔቶች ባለቤትና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ከታሠረ ፤ ጥቅምት 3 ቀን 2008 ዓ.ም አንድ ዓመቱን ደፍኗል፡፡ የተመስገን ጤና አሳሳቢ መሆኑን ቤተሰቡቹ ገልጸዋል፡፡ ማረሚያ ቤቱ ግን ተመስገን ሕክምና እያገኘ መሆኑን ጤናማም እንደሆነ ይናገራል፡፡

የተመስገን ደሣለኝ ታናሽ ወንድም ታሪኩ ደሣለኝ ተመስገንን ረቡዕ፤ ጥቅምት 3 ቀን 2008 ዓ.ም ዝዋይ ሄዶ መጎብኘቱንና፣ ወንድሙ የግራ ጆሮው ሙሉ በሙሉ እንደማይሰማ፣ ጀርባው ላይ ያለው እብጠት እየባሰበት መሆኑን በጀርባው መተኛትም እንደማይችል አስረድቷል፡፡
ተመስገን ማረሚያ ቤቱ ውስጥ ሕክምና እንደማያገኝና ቤተሰቡም ለማሳከም ቢጠይቅም ፍቃድ መነፈጉን፣ ጉዳዩን ወደ ፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ይዘው ሄደው “በማረሚያ ቤቱ ጉዳይ ጣልቃ አንገባም” የሚል መልስ ማግኘታቸውን ታሪኩ ለቪኦኤ ገልጿል፡፡
ተመስገን ያዘጋጃቸው ከነበሩት መፅሔቶች በአንዱ ላይ አምደኛ የነበሩት የሕግ ባለሙያ ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያምም ከጥቂት ወራት በፊት ከፕሮፌሰር መስፍንና ከሌሎች ሁለት ሰዎች ጋር ሆነው እዚያው ዝዋይ ድረስ ሄደው እንዳዩትና በወቅቱ የግራ ጆሮው ይደማ እንደነበር ገልፀዋል፡፡
የተመስገን ደሣለኝ ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንንም የዛሬ ሦስት ወር አካባቢ ዝዋይ ሄደው ያዩት መሆናቸውንና በቦታው ርቀት ምክንያት ከዚያ በኋላ በአካል እንዳላገኙት ገልፀው ከቤተሰቦቹ ግን አሁን ያለበትን ሁኔታ እንደሚያውቁ ተናግረዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሕገመንግሥት፣ መንግሥቱ ባወጣቸው ደንቦችና በዓለምአቀፍ ድንጋጌዎችም መሠረት ማንም እሥረኛ ጤንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ መያዝ እንደሚገባው፤ አስፈላጊ በሆነ ጊዜም ሕክምና የማግኘት መብት እንዳለው፤ የማረሚያ ቤቱ አስተዳደርም ሆነ የወህኒ ቤቱ ሃኪም ታራሚው ሕክምና ማግኘቱን የማረጋገጥ ግዴታ እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡
ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ የማረሚያ ቤቱ የፅሕፈት ቤት ኃላፊ ተመስገን አዲስ አበባ ድረስ ተወስዶ ሕክምና ማግኘቱን፤ በማረሚያ ቤቱ ውስጥም እየታከመ መሆኑን፣ ጤናማና እየተንቀሣቀሰ ያለ መሆኑን ገልፀው ጤንነቱ ታውኳል፤ ሕክምና ማግኘት አልቻለም የተባለው ሃሰት መሆኑን ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ተናግረዋል፡፡
ጠበቃው አቶ አምሃ ግን አዲስ አበባ ድረስ ሄዶ አለመታከሙን፣ ሄዶ ቢሆን ኖሮ እርሣቸው ያውቁ እንደነበር ተናግረዋ የማረሚያ ቤቱን የሥራ ኃላፊ መግለጫ አስተባብለዋል፡፡
 

Friday, September 11, 2015

በ2008 ወንድሞቻችን፣እህቶቻችንና ኢትዮጵያ ነፃ የሚወጡበት አመት !!!

በ2008 ወንድሞቻችን፣እህቶቻችንና ኢትዮጵያ
ነፃ የሚወጡበት :የኢትዮጵያ ህዝብየ24ዓመቱን የህወሀት አገዛዝ በቃህ የሚልበት:አመት
 

Sunday, September 6, 2015

የህወሀት እስርና እንግልት ያልበገረው ፍቅር





የህወሀት እስርና እንግልት ያልበገረው ፍቅር

ቂሊንጦ የተካሄደው የቀለበት ስነስርዓት





ብዙ ጊዜ ስለተቃራኒ ፆታ ፍቅር መጻፍ ብዙመ አልወድም ወይም አይመቸኝም ይህ ተከታዩን በቂሊንጦ እስር ቤት ከሰሞኑ የተፈፀመው የቀለበት ስነስርዓት ስሠማ ግን የሆነ የተለየ ነገር ሆኖ ስላገኘሁት ትንሽ ፈለግኩኝ፡፡

ጉዳዩ እንዲህ ነው በተደጋጋሚ ከዚህ ቀደም እዚህ ፌስቡክ ላይ እንደገለፅኩት በአንድ ወቅት የአሁኑ የኢትዮጵያ አየር ሐይል አባል የነበረው ወጣት ሻለቃ አክሊሉ መዘነ የገዢውን ፓርቲ ዘረኝነት እና ጭቆና መቋቋም አቃተኝ በማለት የኢትዮጵያ አየር ሀይልን ከድቶ ኤርትራ በመግባት የትጥቅ ትግል እያካሄደ የሚገኘውን አርበኞች ግንቦት 7 ህዝባዊ ሐይልን ይቀላቀላል ወጣቱ የአየር ሐይል አባል ወደአርበኞች ግንቦት 7 መቀላቀሉን የሠሙት የገዢው ፓርቲ ደህንነቶች በቂም በቀል ተነሳስተው የሻለቃ መዘነ ታናሽ ወንድምን ሠይፈ መዘነን ከሚኖርበት ኮተቤ አካባቢ በመያዝ ወደማዕከላዊ በመውሰድ ከፍተኛ ድብደባ የፈፀሙበት ሲሆን በወቅቱም ይህንን ጉዳይ መረጃ አሰባስቤ ይፋ ማውጣቴ ይታወሳል፡፡ እናም ታናሽ ወንድምዬወን ሠይፈ መዘነን ማዕከላዊ ወስደው ከደበደቡት በኋላ ፍርድ ቤት እንኳን ሳይወስዱ በአሁኑ ሠዓት ቂሊንጦ ወስደው አስረውት ይገኛል አስገራሚው ነገር ሠይፈ መዘነ ከጉዳዩ ጋር ምንም አይነት ግኑኝነት የሌለውና ምንም አይነት ፖለቲካዊ ተሳትፎ ያልነበረውና ስለጉዳዩ ምንም ሳያውቅ በግል ስራ ይተዳደር የነበረ ወጣት ነው፡፡

የሠይፈ መዘነን ወደቂሊንጦ እስር ቤት መዛወር የሠማችው ፍቅረኛው ሚዛን ፎቶው ላይ የምንመለከታት እንስት ጓደኞቿን ሰብስባ ቂሊንጦ እስር ቤት ድረስ በመሄድ ለፍቅረኛዋ ለሠይፈ መዘነ የቃልኪዳን ቀለበት አድርጋለታለች፡፡ በዙሪያዋ የሚገኙ ወጣቶች ሰይፈ በቃ ሻለቃው ወንድሙ አክሊሉ ከድቶ ኤርትራ በመግባቱ የህወሀት ሠዎች ለቂም በቀል ሠይፈን ምን አልባት ለበርካታ አመታት ሊያስሩት ይችላሉ የሚል ማስፈራሪያ ቢሠጧትም አሉባልታውንና ማስፈራሪያውን ችላ ብላ ከሠሞኑ ለሠይፈ መዘነ ቀለበት አድርጋለት እንዲህ ብላው ከቂሊንጦ እስር ቤት ለቃ ሄዳለች ""እውነት ማሸነፏ አትቀርም ያኔ አንተ ነፃ ትወጣና የቃልኪዳን ቀለበታችንወደትዳር ቀለበትነት ትለወጣለች እስከዛው ግን እጠብቅሀለው እወድሀለው""

ምስሉ ላይ የምትመለከቷቸው በአሁኑ ሠዓት ቂሊንጦ በእስር ላይ የሚገኘውን ሠይፈ መዘነን እና ፍቅረኛውን ሚዛንን ነው

Ermias Tokuma Alemayehu 

Thursday, September 3, 2015

የአቶ ሃብታሙ የአቶ አብርሃም ሰሎሞን መለቀቅ ታገደ!!!

የቀድሞው አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ወጣት ሀብታሙ አያሌውና ሌሎች የፖለቲካ አመራሮች  ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንዲፈቱ የሰጠውን ትዕዛዝ የበታች ፍርድ ቤቱ አግዷል፡፡
ፍርድ ቤቱ ውሣኔውን የሰጠው የአቃቤ ሕግን አቤቱታ ተቀብሎ ነው፡፡
ጉዳዩ ያስቀርብ ወይም አያስቀርብ እንደሆነ ለማየትም ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ ሰጥቷል፡

Thursday, May 21, 2015

ህዝባዊ እምቢተኝነት ያብብ ይለምልም!




ለኢትዮጵያ ህዝብ በሙዚቃው በተላለፈው ጥሪ የ24ዓመቱን የህወሀት አገዛዝ በቃህ የሚልበት ጊዜው ዛሬ ሳይሆን አሁኑኑ ነውገዥው የወያኔ መንግስት ስልጣን ከያዘ ጀምሮ አምስተኛው የኢትዬጲያ ብሄራዊ ምርጫ ይካሄዳል ፡፡ ሶስተኛውና ተስፋ የፈነጠቀው አገራዊ ምርጫ ተስፋ አስቆራጭ በሆነ የፓለቲካ ምህዳር መዘጋት ከተጠናቀቀ በኋላ የተካሄደውን አራተኛው ምርጫ ኢህአዴግ 99.6 በመቶ የፓርላማ መቀመጫ “በማሸነፍ” ተቆጣጥሮታል፡፡ ከቀናት በኋላ የሚካሄደው አምስተኛ አገራዊ ምርጫ የፓለቲካ ምህዳሩን ለማሻሻል የሚረዳና መጠነኛ ክፍተት ሊፈጥር ይችላል ተብሎ ቢጠበቅም በተቃራኒው ገዥው ፓርቲ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በከፍተኛ ሁኔታ እያዳከመ ተቺዎችን እና ሌሎች ነጻ ድምጾችን ለእስር ዳርጎ በከፍተኛ ጫና ታጅቦ ይካሄዳል፡።በቅርቡ ከእስር የተለቀቁት አቶ በቀለ ገርባ በምርጫ ቅስቀሳ ላይ እያሉ ተደበደቡ። ዘረፋም ተፈጽሞባቸዋል። የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር ዶክተርመረራ ጉዲና መንግስት ምጥ ይዞታል። የህዝብ ማዕበል አስፈርቶታል። የለየለት ተናካሽ ወጥቶታል ይላሉ።
_ምርጫው ሲቃረብ አፈናው፡ እስሩ፡ ማሰቃየቱ፡ ማሳቀቁ፡ ግድያው በየአቅጣጫው በርትቷል። ሰማያዊ፡ መድረክና ሌሎች ፓርቲዎች አቤቱታቸውን እያቀረቡ ናቸው። በዚህ መሃል ዕቅድ ያልተያዘላቸው፡ በጀት ያልተመደበላቸው ፕሮጀክቶች መሰረተ ድንጋይ በየቦታው እየተጣለላቸው ነው። አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በዚህም የተነሳ ሰሞኑን ስራ በዝቶባቸዋል።
_አዲስ አብዮተኛ ሙዚቃ ሰሞኑን ለአድማጭ ጆሮ ደርሷል።
ለኢትዮጵያ ህዝብ በሙዚቃው በተላለፈው ጥሪ የ24ዓመቱን የህወሀት አገዛዝ በቃህ የሚልበት ጊዜው ዛሬ ሳይሆን አሁኑኑ ነው!!!

Thursday, April 30, 2015

ኢትዮጵያ በታሠሩ ጋዜጠኞች ብዛት በአፍሪካ አንደኛ ነች

Imprisonment is the most effective form of intimidation and harassment used against journalists.

 

"
ሃሣብን የመግለፅ ነፃነት መብቷን ተግባራዊ በማድረጓ ብቻ ታሥራ የምትገኘውን ርዕዮትን እንዲፈታ ለመንግሥቱ ጥሪያችንን እናቀርባለን - መንግሥቱ ፀረ-ሽብር አዋጁን ሃሣብን በነፃነት የመለዋወጥን ተግባር ለመጠምዘዝ ጉዳይ ከመጠቀም እንዲቆጠብም እናሳስባለን"FREE THE PRESS


Seven of the 10 most censored countries-Eritrea, Ethiopia, Azerbaijan, Vietnam, Iran, China, and Myanmar-are also among the top 10 worst jailers of journalists worldwide, according to CPJ's annual prison census


In Ethiopia--number four on CPJ's most censored list--the threat of imprisonment has contributed to a steep increase in the number of journalist exiles. Amid a broad crackdown on bloggers and independent publications in 2014, more than 30 journalists were forced to flee, CPJ research shows. Ethiopia's 2009 anti-terrorism law, which criminalizes any reporting that authorities deem to "encourage" or "provide moral support" to banned groups, has been levied against many of the 17 journalists in jail there.


How censorship works: As Ethiopia prepared for its May 2015 elections, the state systematically cracked down on the country's remaining independent publications through the arrests of journalists and intimidation of printing and distribution companies. Filing lawsuits against editors and forcing publishers to cease production have left only a handful of independent publications in a country of more than 90 million people. Ten independent journalists and bloggers were imprisoned in 2014; authorities filed a lawsuit in August accusing six publications of "encouraging terrorism," forcing at least 16 journalists to flee into exile. There are no independent broadcasters, though broadcasts from the U.S.-based opposition Ethiopian Satellite Television (ESAT) intermittently air within the country. The state-controlled telecommunications company Ethio Telecom is the sole Internet provider and routinely suspends critical news websites. International journalists work in Ethiopia, but many are under surveillance and face harassment. Although journalists have not had difficulties acquiring accreditation in the past, newer arrivals say that they face challenges.


Lowlight: Authorities in 2014 unleashed the largest onslaught against the press since a crackdown in 2005 after disputed parliamentary elections. Ten independent journalists and bloggers were arrested on anti-state charges, and at least eight independent publications were shut down.


https://cpj.org/2015/04/10-most-censored-countries.php

Friday, April 17, 2015

በኢትዮጵያ የሚታየው የህንጻ ግንባታ የድህነት መሸፈኛ ጭምብል ይሆንን?(Is Ethiopia's building boom masking poverty?


 Is Ethiopia's building boom masking poverty?
Africa blog: Is Ethiopia's building boom masking poverty?

Whenever we set up our camera and flapped open our sun reflectors in Ethiopia's capital, Addis Ababa, passers-by became curious and eager to help.

But getting them to talk on camera was another matter as in general residents of the city are reticent and keep their views to themselves.

We were filming in Addis Ababa for a programme charting the changes in the country, yet it was only on the flight back to South Africa that I met an Ethiopian willing to be candid.

I found myself seated next to an inquisitive elderly Ethiopian woman, who was chatty despite the early morning departure.

However, she was not so open as to be willing for me to mention her name here.

She wore a green twin-set, leggings and woollen socks with her loafers. After the rigorous security checks, she took the socks off, saying she only wears them to keep her feet clean at the end of the security protocols.

She reminded me a bit of my mother, both caring and bossy all in one person.

During the flight, she cut me a portion of her fruit and insisted that I eat every morsel; her stern gaze suggested that I had no choice.
We talked about a lot of things, including my impressions of Nigeria, especially following the ground-breaking presidential election there when the incumbent lost.

She was proud of the manner in which Nigerians had used their vote to make a strong statement about their government.

I replied that perhaps if Ethiopians have strong views about the ruling party - the EPRDF, in power since 1991 - then they could also do the same when elections are held in May. 
http://www.bbc.com/news/world-africa-32310735

Friday, February 6, 2015

የዞን ዘጠኝ ተከሣሾች የመሃል ዳኛው እንዲቀየሩ ጠየቁ!

የዞን ዘጠኝ ጋዜጠኞችና የኢንተርኔት ፀሐፊዎች

እሥር ቤት ውስጥ የሚገኙት ዘጠኝ ጋዜጠኞችና የኢንተርኔት ፀሐፍት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ሰብሳቢ ዳኛ ከዚህ በኋላ ጉዳያቸውን እንዳይመለከቱ ያቀረቡት አቤቱታ ውድቅ ተደርጓል፡፡
አቤቱታ ያቀረቡባቸው ዳኛ ግን በራሣቸው ፈቃድ ጉዳዩን ላለማየት መወሰናቸውን ገልፀዋል።
 
ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ
የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ጋዜጠኞችን ጉዳይ የሚመለከተው የልደታው ችሎት ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚሰጠው ውሳኔ ምን ሊሆን እንደሚችል በጉጉት ሲጠበቅ ነበር። በተለይም ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞቹ የመሃል ዳኛው ስራቸውን በሚገባ እያከናወኑ ስላልሆነ፤ እንዲነሱላቸው ነበር በደብዳቤ የጠየቁትከተከሳሾቹ አንዱ አቤል ዋበላ እሥር ቤት ውስጥ ግፍ እንደተፈፀመበት ለፍርድ ቤቱ አቤት ብሎ መፍትሔ እንዲሰጠው አመልክቷል፡አቤል ዋበላ እንደትላንት ከፍርድ ቤቱ ወደ ቅሊንጦ ማረሚያ ቤት ሲወሰድ፤ ፖሊሶቹ እረስተው በእጁ ካቴና ሳያስገቡ ቀርተው ነበር። ያለካቴና ቅሊንጦ ከደረሰ በኋላ ግን የደረሰበትን ስቃይ ሲያስረዳ በፍርድ ቤቱ ውስጥ የተገኙት በሙሉ አዝነው ነበር። “ቅሊንጦ ስንደርስ እጄ ላይ ካቴና ስላልነበረ፤ የማረሚያ ቤቱ ሰራተኞች እየሰደቡ እና እያንገላቱ እጄን በውሻ ሰንሰለት አስረው ነው ያሳደሩኝ” በማለት እንባ እየተናነቀው ነበር የተናገረው። “ሌላው ቀርቶ ማዕከላዊ እያለሁ በደረሰብኝ ከፍተኛ ድብደባ ምክንያት አንድ ጆሮዬ በደንብ አይሰማም። በመሆኑም ለመስሚያ የሚያገለግለኝን የጆሮ ማዳመጫዬንም ወስደውብኛል” በማለት የደረሰበትን ግፍ እና በደል አስረድቷል።
ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለማየት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
 

Sunday, December 7, 2014

ኢትዮጵያ የኢንተርኔት መብት ከሌላቸው 10 ሀገራት አንዷ እንደሆነች ተገለፀ፡፡

ፍሪደም ኦን ዘ ኢንተርኔት 2014›› የተባለው ሪፖርት ባወጣው ደረጃ መሰረት በ 65 ሀገራት ጥናት በማካሄድ የኢንተርኔት መብት የማይከበርባቸውን የመጀመሪያዎቹን አስር ሀገራት አስቀምጧል፡፡
ከእነዚህ ሀገራት ኢትዮጵያ በአምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች እንደ ሪፖርቱ፡፡
የኢንተርኔት ነፃነት የማይከበርባቸው ሀገራት ተብለው ከተቀመቱት እንደ ኢራን፣ ሶርያ፣ ቻይና፣ ኡዝቤኪስታን፣ ቬትናም፣ ባህሬን፣ ሳውዲ አረቢያና ፓኪስታን ያሉ የእስያ ሀገራት ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡
ከአስሩ ሀገራት ኢትዮጵያና ኩባ ብቻ ናቸው የእሲያ ያልሆኑ የኢንተርኔት መብት የሌላቸው ሀገራት፡፡
ዘገባው IBN Live ነው==>
Pakistan is among the 10 worst countries along with Iran and China on the index of internet freedom, according to a global survey released today.
Freedom House released its 'Freedom on the Internet 2014' report, which surveyed 65 countries and listed the index on obstacles to internet access, limits placed on internet content, and violations of internet user rights.
It showed Pakistan at 10th position, one step down from the 11th worst in 2013, an increase in the restrictions imposed on the internet.

ts gradual fall during the past four years continues when it was 13th from the bottom in 2011.
Majority among the top ten worst countries are from Asia, including Iran, Syria, China, Uzbekistan, Vietnam, Bahrain, Saudi Arabia and Pakistan.
Only Cuba and Ethiopia are two others non-Asian among the top ten, placed at fourth and fifth positions.

Tuesday, November 18, 2014



ከጥቂት ጊዜያት በፊት BecauseIamOromo በሚል ርእስ አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተቋም አምነስቲ ኢንተርናሽናል በኦሮሞ ወጣቶች አራማጆች እና ፓለቲከኞች ላይ የሚደርሰውን ሰፊ የመብት ጥሰት በዝርዝር የሚያሳይ ሪፓርት ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ይህ ሪፓርት በተደጋጋሚ የምንሰማቸው የነበሩትን የኦሮሞ ወጣቶች ላይ የሚደርሱ የመብት ጥሰቶቸን በአስደንጋጭ ሁኔታ እና በሚገባ የዘገበ ነው፡፡ ይህ የመብት ጥሰት ዘገባ በተለያዩ አካላት ርእሰ ጉዳይ ተደርጎ ቢነሳም በቂ ውይይት ሊደረግበት ተጨማሪ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል በሚል እሳቤ ከህዳር 4 እስከ 6 ሶስት ቀናት የሚቆይ የበይነ መረብ ዘመቻ አዘጋጅተናል፡፡ ይህ ዘመቻ የሪፓርቱ ርእስ በሆነው ኦሮሞ በመሆኔ (‪#‎BecauseIamOromo‬) በሚል መሪ ቃል ይካሄዳል፡፡
የዚህ በይነ መረብ ዘመቻ ዋና አላማ በኦሮሞ ህዝብ ላይ በመንግስት በሰፊው ያለማቋረጥ እየተካሄደ ያለው የሰብአዊ መብት ረገጣ ለማውገዝ ፣ በመብት ረገጣው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች አጋርነታችንን ለማሳየትና በጨቋኙ ስርአት በኦሮሞ ህዝብ ላይ እየደረሰ ላለው ቀጣይ የመብት ጥሰት ዝም መባል የማይገባው አገራዊ ጉዳይ አንደሆነ ለማሳየት ነው ፡፡ በዚህ ዘመቻ በዘጋቢ ሪፓርቱ ላይ በሰፊው የተጠቀሱ የኢህአዴግ መንግሰት የፈጸማቸውን የመብት ጥሰቶችንም ለማጋለጥ እና ለማሳወቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለን እናምናለን፡፡ በዚህ ዘመቻ ማስተላለፍ የምንፈልገው መልእክት ግልጽ ነው፡፡ የህዝቦች ወንድማማችነት በጨቋኝ ስርአት ውስጥ ጠንክሮ መታየት እንደገባው በአንድ ብሄር ላይ የተነጣጠረ የመብት ጥሰትም የሁሉም ኢትዮጲያውያን ጉዳይ መሆኑን! አንድ አካል ሲነካ መላ ሰውነትን እንደሚያመው ሁሉ ገዢዎቻችን ለይተው የሚያደርሱት ጭቆና የሁላችንም ህመምና ጉዳይ መሆኑን ለማሳየት በዚሀ ዘመቻ ላይ በንቃት እንድትሳተፉ በአክብሮት ተጋብዛችኋል፡፡
ፌስቡክና ትዊተር በዋናነት የዘመቻው ቦታዎች ሲሆኑ፣ የዘመቻው ተሳታፊዎች በሙሉ #BecauseIamOromo መሪ ቃልን አንዲጠቀሙ ከዘጋቢ ሪፓርቱ እና ከሪፓርቱም ውጪ የሚያቋቸውን ታሪኮች አጭር ጽሁፎች(ስታተሶች) እንዲሁም የተሰማቸውን ስሜት በመግለጽ ለዘመቻው የተዘጋጁ ፕሮፋይል ፎቶዎቸን እና የሽፋን ምስሎችን በመጠቀም በዘመቻው ንቁ ተሳታፊ አንዲሆኑ በአክብሮት አንጋብዛለን፡፡ በሶስቱ ቀን የዘመቻ ቆይታ ለዘመቻው ተብሎ የተከፈተው ኤቨንት ገጽ ላይም ሀሳቦችን በመለዋወጥ እና ስለዘመቻው ያላችሁን ሃሳብ አንድትገልጹ በአክብሮት ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡
አንወያይ ሃሳብና ስሜታችንን እናካፍል ጉዳያችን መሆኑን አጋርነታችንን እናሳይ!
 #ኦሮሞ_በመሆኔ #OromooTauukoof #BecauseIamOromo

Friday, October 31, 2014

የአፍሪካ ጸደይ"ኮምፓዎሬ “ደህና ሁኑ”!!!!!



ቡርኪናፋሶን ያለገደብ ሲመሩ የነበሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ ለተጨማሪ ዓመታት ሥልጣናቸውን ለማራዘም ያደረጉት ሙከራ በመክሸፉ ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ ገለጹ፤ ለአንድ ዓመት የመሸጋገሪያ መንግሥት ተመስርቶ ምርጫ እስከሚደረግ በሥልጣን እንደሚቀጥሉ አስታወቁ፡፡ ሕዝቡና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ግን ይህንን የሚቀበሉበት ትከሻ እንደሌላቸውና የኮምፓዎሬ አገዛዝ አሁኑኑ መውረድ እንዳለበት በተቃውሟቸው እየገለጹ ነው፡፡ ከ27ዓመት አምባገነናዊ ሥርዓት በኋላ ቡርኪናፋሶ ወደ ሌላ አምባገነናዊ ሥርዓት ልትሄድ እንደምትች ተጠቆመ፡፡

በቀድሞው ፕሬዚዳንት ቶማስ ሳንካራ ዘመን የመንግሥት ባለሥልጣንና የሳንካራ ወዳጅ የነበሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ፤ ቶማስ ሳንካራ ባልታወቀ ሁኔታ በመፈንቅለ መንግሥት ከተገደሉ ከዛሬ 27ዓመት ጀምሮ ቡርኪናፋሶን መግዛት ጀመሩ፡፡ መፈንቅለ መንግሥቱን በመምራት የተሳተፉት ኮምፓዎሬ የሳንካራን መገደል በወቅቱ “ድንገተኛ” በማለት ከመጥቀስ በስተቀር ምርመራ እንዲካሄድ አላዘዙም፤ ምስጢሩም እንዳይወጣ ተደርጎ ቆይቷል፡፡

ቶማስ ሳንካራን ከሥልጣን ካስወገዱ በኋላ ለሦስት ዓስርተ ዓመታት ያህል የዘለቀውን አገዛዛቸውን የጀመሩት ኮምፓዎሬ እኤአ በ1990ዎቹ በተደጋጋሚ የተመረጡት ሲሆን የአገሪቱ ሕገመንግሥት ከተሻሻለ በኋላ በሁለት ሺዎቹም ሁለት ጊዜ ተመርጠዋል፡፡

በአገዛዝ በቆዩበት ዘመን ሁሉ የአውሮጳውያንና የአሜሪካ ወዳጅ በመሆን ሥልጣናቸው ሳይደፈር በአምባገነንነት ለመቆየት ችለዋል፡፡ አክራሪ እስላማዊነትን እዋጋለሁ በማለት የአሜሪካ ወዳጅነታቸውን ያጠናከሩት ኮምፓዎሬ በላይቤሪያና ሴራሊዮን እጅግ አስከፊ ጭፍጨፋ ያካሄዱትን እና በአሁኑ ወቅት 50ዓመት እስራት የተበየነባቸው የቀድሞው የላይቤሪያ መሪ ቻርልስ ቴለር የቅርብ ወዳጅ ነበሩ፡፡ ሳንካራን ለመገልበጥና ለመግደል የቴይለር ጦር እንደተሳተፈና በምላሹ ኮምፓዎሬ ለቴይለር ወደ ሥልጣን መምጣትና ከዚያ ጋር ተያይዞ ለተፈጸመው ወንጀል ተባባሪ ናቸው በማለት ሁኔታዎችን የሚያገናኙ ወገኖች አሉ፡፡

በአገራቸው የሚነሱ ተቃውሞዎችን ስልታዊ በሆነ መንገድና በምዕራባውያን ድጋፍ ሲያከሽፉ የኖሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ በአካባቢው አገራት ዘንድ የሰላም ዘንባባ አቅራቢ፣ አስታራቂ፣ አስማሚ፣ ሸምጋይ፣ … ሆነው ምስላቸውን እና ማንነታቸውን ሲገነቡ ቆይተዋል፡፡ በአምባገነንነት በቆዩባቸው ዓመታት በሙስና በተለይም ከአልማዝ ሽያጭ ከሚገኘው ገንዘብ ያላቸው ተሳታፊነት ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል፡፡

በቀጣዩ የአውሮጳውያን ዓመት 2015 ሥልጣናቸው የሚያበቃው ኮምፓዎሬ “ደህና ሁኑ” ብለው ለመሄድ የተዘጋጁ አልነበሩም፡፡ በመሆኑም የአገሪቱን ሕገመንግሥት በማሻሻል እንደገና ለመመረጥ ደፋ ቀና ማለት ጀመሩ፡፤ ፓርላማቸውን አሰብስበው ሕገመንግሥቱ እንዲሻሻል በማድረግ ሂደት ላይ እያሉ ሕዝቡ “በቃኝ” አለ፡፡

የ27 ዓመታት አገዛዝ የመረራቸው ዜጎች ሐሙስ ዕለት ፓርላማውን ጥሰው በመግባት ድምጽ እንዳይሰጥ ከማድረግ አልፈው በእሣት አጋዩት፡፡ ተቃውሞ በየቦታው ፈነዳ፡፡ ቡርኪናፋሶ መጋየት ጀመረች፡፡ ሁኔታው ያላማራቸው ኮምፓዎሬ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጁ፡፤ ሰሚ ግን አላገኙም፡፡ ሕዝቡ “ይህንን አገዛዝ አንፈልግም፣ በቃን” አለ፡፡ ሕዝባዊ ዓመጽ በየቦታው ተቀጣጠለ፡፡ በተለይ ዋና ከተማዋ ዖጋዱጉ የዓመጹ ዋና ማዕከል ሆነች፡፡

መንግሥት ሥራ አቆመ፣ ፓርላማውም ፈረሰ፡፡ ድህነት ያስመረራቸው ዜጎች አሁንም ተቃውሟቸውን ቀጥሉ፡፡ ኮምፓዎሬን ማየትም ሆነ መስማት በጭራሽ አይፈልጉም፡፡ ወታደሮች በየአካባቢው ሥነሥርዓት ለማስጠበቅ እየጣሩ ቢሆንም ዓመጹ ግን ቀጥሏል፡፡ ንብረት እየወደመ ነው፤ ባንኮችም ተዘርፈዋል፡፡

ዛሬ አርብ ዳግም ለመመረጥ ሲመኙ የነበሩት ኮምፓዎሬ ሥልጣን በቃኝ፤ መንግሥት ፈርሷል፤ ፓርላማውም አይሰራም፤ ከሥልጣኔ እለቃለሁ ነገር ግን በ2015 ምርጫ እስከሚካሄድ የሽግግር አስተዳደር ተመስርቶ ሁሉም ነገር መረጋጋት አለበት በማለት አስቀድሞ በተቀዳ የቴሌቪዥን መልዕክት ቢያስተላልፉም ሰቆቃ የመረራቸው፣ ኑሮ ያቃጠላቸው፣ ነጻነት የጠማቸው ዜጎች ግን አሁንም “አንሰማም” ብለው ተቃውሟቸውን በመቀጠል ፕሬዚዳንቱ ከሥልጣን እንዲወርዱ ጠይቀዋል፡፡

ሰላሳ አራት የሚሆኑ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ፕሬዚዳንቱ ያቀረቡትን ቅደመ ሁኔታ አንቀበልም ብለዋል፡፡ ለኮምፓዎሬ ምላሽ ሲሰጡም “አንድ የምንቀበለው አጭርና ግልጽ ቅድመ ሁኔታ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ብሌዝ ኮምፓዎሬ ከሥልጣን እንዲለቁ ነው” በማለት ተናግረዋል፡፡

ጦሩ ሥልጣኑን የተረከበ እንደሆነ እየተጠቆመ ሲሆን አገሪቱን በበቂ ሁኔታ ለማረጋጋት እንዳልቻለ ከዋና ከተማዋ የሚመጡ ዜናዎች ይጠቁማሉ፡፡ የሕዝቡ ዓመጽም ወደ ሌሎች ከተሞች እየተዛመተ መሆኑን ከተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች እየተሰማ ነው፡፡

በአንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ዘንድ ከአረብ ጸደይ ቀጥሎ የተጀመረ “የአፍሪካ ጸደይ” ሊሆን ይችላል በማለት ግምት የሰጡበት የቡርኪናፋሶ ሕዝባዊ አመጽ ተመልሶ በአምባገነናዊ አገዛዝ እንዳይወድቅ ስጋት አላቸው፡፡ ለዚህም ጠንካራ ተቋማት መመሥረት አስፈላጊነትን ያሰምሩበታል፡፡ በተለይ ከአምባገነናዊ አገዛዝ ወደ ሕዝባዊ ሥርዓት በሚደረግ ጉዞ በቅድሚያ የሚደረጉ መሰናዶዎች ሳይከናወኑ በጭፍን አምባገነኖችን ከሥልጣን እንዲወርዱ ማድረግ በበርካታ አገራት እንደተደረገው መልኩን የቀየረ አምባገነናዊ ሥርዓት ለመመሥረት እንደሚጋብዝ ይናገራሉ፡፡ ከዚህ አንጻር የሕዝብ ንቃተ ኅሊና መዳበር፣ የእርሰበርስ ውይይት መጀመር፣ የተቋማት መመሥረት፣ … ወሳኝነት ያላቸው ቅድመ ሁኔታዎች እንደሆኑ ያሰምሩበታል፡፡

ይህንን ዘገባ ካጠናቀርን በኋላ ከቢቢሲ የተገኘው ዜና እንደሚያመለክተው ከሆነ ፕሬዚዳንቱ ሥልጣናቸውን ጥለው ከአገር እየወጡ እንደሆነ የጦሩ ጄኔራል ዖኖሬ ትራዖሬ በሕገመንግሥቱ መሰረት አገሪቷን እየመሩ እንደሆኑ አስታውቀዋል፡፡ የፕሬዚዳንቱ ቦታ ባዶ እንደሆነና በ90 ቀናት ውስጥ ምርጫ እንዲካሄድ መነገሩን ቢቢሲ ጨምሮ ዘግቧል፡፡ ብሌዝ ኮምፓዎሬ አሁን ያሉበት ቦታ ባይታወቅም በአቅራቢያ ባለ አገር አቋርጠው ወደ አንድ አውሮፓ ምናልባትም ፈረንሳይ የስደት ህይወታቸውን መምራት ይጀምራሉ የሚል ግምት እንዳለ እየተነገረ ነው፡፡