Monday, August 25, 2014

መለስን ቅበሩት!



መለስን ቅበሩት!

ከኢትዮጵያ ሀገሬ የደቀቀ ኢኮኖሚ ላይ በማን አህሎኝነት ወጪ ተደርጎ፣ ቅጥ ባጣ መልኩ በመላ አገሪቱ እየተከበረ ስላለው የቀድሞ አምባገነን ጠ/ሚኒስትር ሁለተኛ ሙት ዓመት ዝክርም ሆነ ሰውየውን ዛሬም በአፀደ-ህይወት ያለ ለማስመሰል እየሞከሩ ላሉት ጓዶቹ አንዲት ምክር ብጤ ጣል ማድረጉ ተገቢ ነው ብዬ ስለማስብ በአዲስ መስመር እንዲህ እላለሁ፡-

አብዮታዊው ገዥ-ግንባር ግንቦት ሃያ፣ የህወሓት ምስረታ፣ የብአዴን አፈጣጠር፣ የኦህዴድና የደኢህዴን ውልደት፣ የብሔር ብሔረሰቦች በዓል፣ የባንዲራ ቀን፣ የመከላከያ ሳምንት፣ የፍትሕ ሳምንት፣ የሕዳሴ ግድብ መሰረት ድንጋይ የተጣለበት… ጅኒ-ቁልቋል እያለ ዓመቱን ሙሉ በማይጨበጥ ተራ ፕሮፓጋንዳ ማሰልቸትን መንግስታዊ ኃላፊነት አድርጎታል፡፡ ይህ እንግዲህ ለቁጥር የሚያታክቱ፣ በነጭ ውሸት የታጨቁ እና በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ቅኝት የተንሸዋረሩ ‹ዶክመንተሪ ፊልሞቹ›ን ረስተንለት ነው፡፡


ይህ ሁሉ ያልበቃው ‹‹ጀግናው›› ኢህአዴግ ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ህልፈት ወዲህ፣ ወርሃ-ነሐሴንም እንደ ግንቦት ሃያው ሁሉ የሟቹን ታጋይነትና አብዮታዊነት፤ ሕዝባዊነትና አርቆ አስተዋይነት፤ የርዕዮተ-ዓለም ተራቃቂነትና የአየር ንብረት ተካራካሪነት፤ በፖለቲካ ቢሉ በኢኮኖሚ ቁጥር አንድ ጠቢብነትና ባለራዕይነት፤ ፍፁም ፃድቅነትና ሰማዕትነት…. የሚተረክበት ሲያደርገው ቅንጣት ታህል ሀፍረት አልተሰማውም፡፡ ሰሞኑን በ‹‹ኢትዮጵያ›› ቴሌቪዥን ግድ ሆኖብን ተመልክተንና ሰምተን በትዝብት ካሳለፍናቸው
‹‹መለስ፣ መለስ›› ከሚሉ የከንቱ ውዳሴ አደንቋሪ ድምፆች በተጨማሪ፣ የኦሮሞን ባሕላዊ ልብስ ሲያለብሱት፣ ሐረሪዎች ጋቢ
ሲደርቡለት፤ በደቡብ የሚገኙ ብሔሮች የየራሳቸውን ባሕል የሚወክሉ አልባሳት ሲሸልሙት፣ ስለወላይታነቱ ሲመሰክሩለት… ደጋግመን ለመመልከት ተገደናል፤ ይሁንና ድርጅቱ ስለ ቀድሞ ሊቀ-መንበሩ አልፋና ኦሜጋነት ለመስበክ ዙሪያ ጥምዝ ከዳከረለት ከእንዲህ አይነቱ የተንዛዛ ፕሮፓጋንዳ ይልቅ፣ በዚሁ የቴሌቪዥን መስኮት የቀረበ አንድ ጎልማሳ ‹‹መለስ ሁሉም ማለት ነው›› ሲል የሰጠው አስተያየት፣ ቅልብጭ አድርጎ ይገልፅለት ነበር ብዬ አምናለሁ፡፡ የዚህ አይነቱ ምጥን አስተያየትም በጥራዝ ነጠቅነት ዘላብዶ የኋላ ኋላ በሀፍረት ከማቀርቀር ያድናል፡፡ ለምሳሌ እናንተ የግንባሩ ካድሬዎች ስለመለስ ምሁርነት ለመናገር ስትዳዱ ሁሌ የምትደጋግሙት፣ ያንኑ
የአብዮታዊ ዴሞክራሲ አርቃቂነቱ እና የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ኀልዮት አዋቃሪነቱ ነው፡፡ ግና፣ ይህ ‹‹ንድፈ-ሃሳብ›› ተብዬ ራሱ በርዕዮተ-ዓለምነት ለመጠራት የማይበቃ የተውሸለሸለ ጭብጥ ስለመሆኑ በርካታ ምሁራን በጥናቶቻቸው ከማስረገጣቸው ባሻገር፣ አገሪቷን ለከባድ ኢኮኖሚያዊ ድቀት፣ ሕዝቧን ደግሞ ለጥልቅ ድህነት መዳረጉን ብቻ ማስታወሱ በቂ ይሆናል፡፡ ስለልማታዊ መንግስት አዋጭነት በብቸኝነት እንደተከራከረ ተደርጎ የሚለፈፈውን እንኳን ንቆ መተው ሳይሻል አይቀርም፡፡ ከታንዲካ ማካንደዋሬና መሰል የፅንሰ-ሃሳቡ አበጂዎች የዘረፋቸውን መከራከሪያዎች ማን ዘርዝሮ ይዘልቀውና፡፡ ‹መለስን ቅበሩት› የምለውም፣ እንዲህ ያሉ አስነዋሪ ማንነቶቹን ማስታወስ ስለሚያም ነው፡፡

እናም እውነት እውነት እላችኋለሁ፡- ስለሰውዬው የምትነግሩን እና የምታስቀጥሉት ‹ሌጋሲ›ም ሆነ የምትተገብሩት ረብ ያለው አንድም ራዕይ የለምና ዝም፣ ፀጥ ብላችሁ የምራችሁን ቅበሩት፡፡ እስቲ! ኦጋዴንን ተመልከቱ፤ ካሻችሁም ወደ አኝዋኮች ተሻገሩ፤ ያን
ጊዜ እናንተ በአርያም የሰቀላችሁት ሰው፣ ለነዚህ ሁለት ብሔሮች የቀትር ደም የጠማው ጨካኝ መሪ እንደነበር፣ በክፋት ትዕዛዞቹ ጥፋት ከተረፈ ጠባሳ ትረዱታላችሁ፡፡ ለአቅመ-ሔዋን ያልደረሱ ህፃናት በሰልፍ የሚደፈሩባት፣ ወጣቶች እንጀራ ፍለጋ በተስፋ-ቢስነት ጥልቁን ውቅያኖስ ሰንጥቀው ለመሰደድ የማያመነቱባት፣ የጤና ኬላ ማግኘት ተስኗቸው በልምሻ የሚባትቱ ብላቴኖችን በአቅም-የለሽነትና በቁጭት የምናስተውልባት ደካማ አገር አስረክቦን እንዳለፈ ከወዴት ተሰወረባችሁ? ከቀዬዎቻቸው በጉልበት ለተፈናቀሉ ወገኖች በመቆርቆር ‹‹ሕግ ይከበር!›› ባሉ በየጉራንጉሩ ወድቀው እንዲቀሩ የተፈረደባቸው ጎበዛዝትን ሬሳ እንድንቆጠር ያደረገን ደመ-ቀዝቃዛ
‹መሪ› እንደነበረስ ስንት ጊዜ እያስታወስን እንቆዝም? ቀደምት አባቶች ወራሪውን ፋሽስት ለማንበርከክ የተዋደቁባቸው ጢሻና ኮረብቶች በዚህ ዘመን የዜጎች ወደሞት አገራት መሸጋገሪያ ጽልማሞቶች የሆኑት በማን ሆነና ነው? ከሕግ ተጠያቂነት ቢያመልጥ፣ ከታሪክ ተወቃሽነት ልትታደጉት የምትችሉ ይመስላችኋልን?

…ይልቅ እመኑኝ! ፀጥ ብላችሁ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ጥልቅ ጉድጓድ ቆፍራችሁ ቅበሩት! ላይመለስ በመሄዱም እንደ ግልግል ቆጥራችሁት እርሱት!! መቼም በገዛ ራሱ ሕዝብ ላይ ትውልዶች ይቅር ሊሉት የሚሳናቸውን ይህን መሰሉ መከራ ላዘነበ ሰው በአፀደ- ስጋ ሳለም ሆነ በበድን የሙት መንፈሱ ስር በየዓመቱ ለአምላኪነት መንበርከክ፣ የናንተን አልቦ ማንነት እንጂ ሌላ አንዳች የሚነገረን ቁም ነገር ጠብ ሊለው አይችልም፡፡ ይህም ሆኖ ለመለስ አምልኮ እጅ መስጠት አሳፋሪነቱ፣ ለካዳሚዎቹ ብቻ መሆኑን መስክሮ ማለፉ የቀሪዎቻችን ዕዳ እንደሆነ መገንዘብ አለብን፡፡


ተመስገን ደሳለኝ

Friday, August 22, 2014

ዶ/ር መረራ ጉዲና ከቪኦኤ ጋር ያደረጉትን ቃለ-ምልልስ

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ መሪ ዶ/ር መረራ ጉዲና ባለፈው ሣምንት መጨረሻ ዋሺንግተን ዲሲ ውስጥ በሚገኘው ናሽናል ኢንዶውመንት ፎር ዴሞክራሲ በሚባለው ተቋም ውስጥ ለተሰበሰቡ ታዳሚዎች ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡
የዶ/ር መረራ ወረቀት ርዕስ፡- የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር አንድ እርምጃ ወደፊት፤ ሁለት እርምጃ ወደኋላ” የሚል ነው፡፡
ዶ/ር መረራ በዚህ ፅሁፋቸው ውስጥ ያለፉት 23 የኢሕአዴግ ዓመታት በሦስት ዋና ዋና መንገዶች ፡…ያልተሣኩ ነበሩ…” ብለዋል፡፡
በ23ቱ ዓመታት መጀመሪያ ላይ የተነሡት ሥሉስ ቃላት - “ጎሣን መሠረት ያደረገ ፌደራላዊ ሥርዓት፤ ብዝኀ ፓርቲ ዴሞክራሲና የነፃ ገበያ ምጣኔ ኃብት - አልተከበሩም፤ የከሸፉ ቃላት ሆነዋል” ብለዋል፡፡
መጭውን ምርጫ አስመልክቶ ዶ/ር መረራ ሲናገሩ ተቃዋሚዎች በቀረው ጊዜ ተቃዋሚዎች እንዲተባበሩና ጥንካሬን እንዲፈጥሩ መክረዋል፡፡
ዶ/ር መረራ ጉዲና ከቪኦኤ ጋር ያደረጉትን ቃለ-ምልልስ ሙሉ ቃል ያዳምጡhttp://amharic.voanews.com/content/ethiopia-politics-interview-with-dr-merera-gudina-of-medrek-07-19-14/1961194.html

Thursday, July 17, 2014

ሰበር ዜና:- ጦማሪያኑና ጋዜጠኞቹ ላይ ክስ ተመሠረተ



ሰበር ዜና:- ጦማሪያኑና ጋዜጠኞቹ ላይ ክስ ተመሠረተ

በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ውለው የነበሩት ጦማሪያን፣ ሶልያና ሽመልስ (በሌለችበት)፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ አጥናፉ

ብርሃኔ፣ ዘለዓለም ክብረት፣ አቤል ዋበላ፣ እንዲሁም ጋዜጠኞቹ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሣዬና ተስፋለም ወልደየስ ላይ ሐምሌ 10 ቀን 2006 ዓ.ም. ክስ ተመሠረተ፡፡





እኔን ያልገባኝ ተሸባሪው ማነው?ያወራ አሸባሪ የፃፈ አሸባሪ ተቃወሚወች አሸባሪ ህዝቡ ሀሉ አሸባሪ ከሆነ ማነው ተሸባሪ?
 
 
 

Saturday, July 5, 2014

የዓለም ባንክ በተያዘው አመት በታሪኩ ከፍተኛ የገንዘብ መጠን ለኢትዮጵያ ማስተላለፉ ተገለጸ!

 


የዓለም ባንክ በተያዘው አመት በታሪኩ ከፍተኛ የገንዘብ መጠን ለኢትዮጵያ ማስተላለፉ ተገለጸ

መቀመጫውን በዋሽንግተን ያደረገው የዓለም ባንክ በተያዘው ዓመት ባንኩ በታሪኩ ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ድጋፍ እና እርዳታ ማድረጉን የሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ አመልክቷል፡፡

ጋዜጣው በተያዘው ዓመት ብቻ የዓለም ባንክ 1.6 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ለኢትዮጵያ ማስተላለፉን ጠቅሷል፡፡
እኔ የምለው ከዓለም በድህነት 2ኛ?የሄ ሁሉ ገነዘብ የትገባ'?

Tuesday, July 1, 2014

BREAKING NEWS]OLF merged under leadership of Dawud Ibsa with Dhugassa Bakako as deputy!

OLF declares a merge between OLF-QC and OLF-SG

June 28, 2014 (Oromo Liberation Front) — It is with great pleasure that we announce to our people and the supporters of our struggle for freedom the good news that, based on the accord they made in Kampala, Uganda, in November 2012, the two organizations of the Oromo Liberation Front (OLF) known as OLF Shanee Gumii (”OLF National Council”) and OLF Qaama Ce’umsaa (”OLF Transitional Authority”) have resolved our differences and agreed to combine our two leaderships, unify our members, merge our organizational structures and inaugurate a reunified OLF. Although OLF has encountered many obstacles during the last forty years, there was no time when it has stopped the struggle that it was established to lead. No one can deny the fact that the national struggle led by the OLF has scored many victories and made many significant achievements that have taken the Oromo people a long way toward the national goal of independence. Among these great achievements is the level of political awareness of our people.
At the same time, we witness that the Oromo people are being targeted for extinction more than any time before. Oppression has reached intolerable levels making our people to rise up in defiance of tyranny, protesting peacefully in all corners of Oromia. But, as witnessed in the killings of students and others in many places in Oromia, the TPLF regime is responding violently to their lawful demands. Defying enemy atrocities, imprisonment, and torture the young Oromo generation are making it known to the world that they will not tolerate humiliation and oppression anymore and that they will make the necessary sacrifices to liberate their people and homeland from alien oppressors. The OLF extends its condolences to families who lost their beloved sons daughters and expresses its admiration for the courage and bravery they have shown by the young Oromo generation to defend their people’s legitimate rights. As the vanguard of the Oromo struggle for freedom, we re-iterate our determination to continue the struggle until our people become masters of their destiny.
The re-unification of the two organizations of the OLF is a great step that will strengthen the Oromo struggle for freedom. United under one leadership, we are resolute to realize the principal objective of our struggle, namely the liberation of our people and the independence of our homeland Oromia. There is no question about the popularity of the goal of OLF-led liberation struggle among the Oromo people. Therefore, it is with determination that we pledge to make the necessary sacrifices, withstand the challenges ahead and carry through the Oromo national struggle to the ultimate goal of independence.
We are well aware that there are Oromo nationals who are organized separately under other names to advance our people’s legitimate rights. We will do all we can to coordinate our efforts with them to achieve the common goal. The OLF leadership states its decision and commitment to continue to work and conclude the ongoing talks with other forces committed to the same goal. Hence we call on all Oromo organizations that uphold our people’s right to self-determination and independence to join us in carrying out this sacred mission.
We also take this opportunity to express our solidarity with the oppressed nations, nationalities and peoples who are struggling for justice against the same tyrannical regime, and call upon them to join us in the common struggle for basic human and democratic rights.
The TPLF-led regime’s violence against the Oromo people is abetted by military, political and economic assistance from external powers. The OLF appeals again to governments, both in the West and East to strike a balance between their national interests and their international obligation of protecting human rights and stop giving economic, military and political support to a brutal regime that is evicting our people and others from their land and killing innocent civilian who are peacefully demanding their legitimate rights.
Victory to the Oromo People!
Oromo Liberation Front
June 28, 2014

Monday, June 9, 2014

ነቀምቴ ላይ አራት ከፍተኛ ሐኪሞች ታሥረዋል?

ዶ/ር አዳም ለማ፤ የቀዶ ሕክምና ሐኪም፣ ዶ/ር ኢሣያስ ብርሃኑና ዶ/ር በላይ ቤተማርያም የማኅፀንና የፅንስ ስፔሻሊስቶች፣ ዶ/ር ታመነ አበራ፤ ቀድሞ የሆስፒታሉ የሕክምና ዳይሬክተርና አሁን ለስፔሻላይዜሽን የጥቁር አንበሣ ሬዚደንት ሐኪም፣ እንዲሁም ዶ/ር ሪም ጆንግ ሆ፤ ኮርያዊ የአጥንት ሐኪም፡፡
ሁሉም በነቀምቴ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ አገልግለዋል፡፡

ዛሬ ኮርያዊው ሐኪም ከሥራ ሲሠናበቱ አራቱ ኢትዮጵያዊያን ግን በቁጥጥር ሥር ውለው ነቀምቴ በሚገኘው ማረሚያ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፡፡

የእነዚህ ለረዥም ዓመታት አገልግሎት ሰጥተዋል የሚባሉ ሐኪሞች ከሥራቸውና ከደመወዛቸው መታገድ፣ አልፎም መታሠር መነጋገሪያ እየሆነ ነው፡፡

“ጥፋታቸው” የተባለው ምን ይሆን? በአካባቢያቸው ያሉ ሰዎችስ “ጥፋተኛ ናቸው” ብለው ያምናሉ?

የተያያዘው ዘገባ የፖሊስን፣ የሆስፒታሉን አስተዳደር፣ የእሥረኞቹን ሐኪሞች ቤተሰቦችና ጠበቃ የሚሉትን ይዞ ዝርዝር መረጃ ይሰጥዎታል፡፡
ያዳምጡት፡

ቪኦኤ

http://amharic.voanews.com/content/nekempte-doctors-arrested/1635248.html 

ጥፋተኛ ናቸው” ብለው ያምናሉ? ????

 

Wednesday, May 28, 2014

ከግንቦት ሃያ ፍሬዎች?



There are tentative signs that the people of Ethiopia are beginning to organize themselves and stand up against the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) government, a brutal dictatorship, albeit one dressed in Western democratic garb.

After 23 years of suppression at the hands of the EPRDF, simmering discontent and anger appear to finally be spilling over onto the streets. Robbed of hope, the people have had enough, enough of the wide-ranging human rights abuses, the denial of constitutional rights, the arbitrary imprisonments and torture, the regime violence, the displacement of people from ancestral land, the partisan distribution of aid and the rising cost of living.

The government’s heavy-handed reaction to the Oromo protests is but the latest example of the regime’s ruthless response to criticism of its policies. Political opposition parties, when tolerated at all, have been totally marginalized, dissenting independent voices are quickly silenced and a general atmosphere of fear is all pervading. Despite freedom of expression being a constitutional right, virtually all media outlets are either government owned or controlled; “blogs and internet pages critical of the Ethiopian government are regularly blocked and independent radio stations, particularly those broadcasting in Amharic and Afan Oromo, are routinely jammed,”Human Rights Watch says.

The EPRDF has created “one of the most repressive media environments in the world”. Reinforcing this condition, “the government on 25 and 26 April arbitrarily arrested nine bloggers and journalists in Addis Ababa. They remain in detention without charge,” Human Rights Watch reports.

International human rights groups (whose activities have been severely restricted by the stifling Charities and Societies Proclamation of 2009) as well as foreign journalists are not welcome, and reporters who attempt to reach demonstrations are turned away or detained, making it difficult to confirm the exact numbers of those killed by government security personnel.

The UN Human Rights Council recently reviewed Ethiopia’s human rights record under the Universal Periodic Review.

Since the first review in 2009 the human rights situation has greatly deteriorated. The EPRDF rules the country through fear and intimidation, it has introduced ambiguous, universally condemned legislation to control and intimidate – the Charities and Societies Proclamation law and the Anti-Terrorism Proclamation especially.

Freedom of assembly – another constitutional right – is not allowed or, as can be seen with the Oromo protests, is dealt with in the harshest manner possible.

The Internet and telecommunications are controlled and monitored by the government and phone records and recordings are easily obtained by security personnel.

Arbitrary arrests and false Imprisonment of anyone criticizing the government is routine as is the use of torture on those incarcerated.

In the Ogaden region the regime is committing gross human rights abuses which constitute crimes against humanity, and in Gambella and the Lower Omo Valley large numbers of indigenous people have been forcibly moved into government camps (villagization programme), as land is sold for pennies to international companies.

In short, human rights are completely ignored by the government in Ethiopia.

As the people begin to come together and protest, international pressure should be applied on the regime to observe the rule of law and uphold the people’s fundamental human rights.

We are living in extraordinary times, times of opportunity and change, times of great hope. With elections due next year, now is the time for the various ethnic groups and factions inside and outside Ethiopia to unite, speak with one voice and demand their rights to freedom and justice.